ESAT (ኢሳት🇪🇹)®
الذهاب إلى القناة على Telegram
ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot 🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹
إظهار المزيد2025 عام في الأرقام

221 247
المشتركون
-14824 ساعات
-6057 أيام
-2 63230 أيام
أرشيف المشاركات
Photo unavailableShow in Telegram
መኪናዎን #በአስቸኳይ መሸጥ ከፈለጉ ከታች የተዘረዘሩትን መረጃዎች 👇👇ሞልተው
☎️🦈🏌🏽♀ 0911407105 🔫 ላይ ደውለዉ ያሳውቁን። ስለመረጡን እናመሰግናለን👏
➕የመኪናው ዓይነት___
🔤የመኪናው ሞዴል___
➕ትራንስሚሽን___
🔤የዞረ/ያልዞረ___
🧮የተነዳው ኪ.ሜ___
🧮ስለመኪናው አቋም አጭር ማብራሪያ___
🔤በተለያየ አቅጣጫ የተነሳ ፎቶ___
🔤የመሸጫ ዋጋ___
🔤የባለቤት ስልክ___
🎱 0911407105 🔫 ይደውሉልን
➧ቻናላችንን በመቀላቀል የተለያዩ አዳድስና ያገለገሉ መኪኖችን ማግኘት 🫴 Link ይችላሉ !!!
https://t.me/Poppycarmarket
❤ 26🔥 2
Photo unavailableShow in Telegram
መርካቶ ቲቪ ጀመረ!!
ቤትዎ ሆነው መገበያየት፣
በቅናሽ ዋጋ ፣
እቤትዎ ደረስ
በፓርኪንግ ሂሳብ
እንኳን ደስ አሎት የምንለው አሁን ነው
ቲቪ በማየት ብቻ ቤትዎ ሆነው በርካሽ ዋጋ ይገበያዩ
Frequency: 11545
Symbol rate : 45000
Polarization : Horizontal
Join Us on Ethiosat
የመርካቶ ቤተሰብን ይቀላቀሉ
https://t.me/MerkatoTv1
መርካቶ ቲቪ የእናንተ!!
እትዮጵያ ታምረት አፍሪካ ትሸምት!!
❤ 32
Photo unavailableShow in Telegram
በነዳጅ ምርቶች ላይ አጠቃላይ የ30 በመቶ ግብር በተያዘው በጀት ዓመት ተግባራዊ መደረግ ይጀምራሉ ተባለ‼️
የገንዘብ ሚኒስቴር ከ2018 የበጀት ዓመት ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ አጠቃላይ 30 በመቶ ግብር ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ እንደሚያደርግ ማረጋገጡ ተሰማ። ይህ አዲስ ግብር 15 በመቶ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እና 15 በመቶ የኤክሳይዝ ቀረጥን የሚያካትት መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ይህ እርምጃ በአገሪቱ የፋይናንስ ፖሊሲ ላይ ከፍተኛ ለውጥ የሚያመጣ መሆኑና የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አንዱ አካል እንደሆነ ተመላክቷል።
ሚኒስትሩ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ባቀረቡት አጠቃላይ የዜጎች በጀት ዉስጥ፣ በተያዘው በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚደረጉ የግብር አይነቶችን በዝርዝር አስቀምጠዋል።
በዚህ መሰረት፣ ከነዳጅ ላይ ከሚጣለው አጠቃላይ 30% የኤክሳይዝ ታክስ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ በተጨማሪ፣ የንብረት ታክስ ይገኙበታል። እንዲሁም አማራጭ አነስተኛ ታክስ እና የቅድመ ግብር ክፍያ በተመሳሳይ መልኩ በ2018 በጀት ዓመት ተግባራዊ ለማድረግ መታቀዱን ካፒታል ጋዜጣ ለመረዳት ችሏል።
ነዳጅ በማዕከላዊነት የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ የግብር ጭማሪው የዋጋ ግሽበቱ እንዲባባስ ያደርጋል የሚል ስጋት ሲከሰት እንደነበር ይታወሳል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
❤ 164😡 54😁 13👏 8👍 6🔥 3🤝 3
Photo unavailableShow in Telegram
መርካቶ ቲቪ ጀመረ!!
ቤትዎ ሆነው መገበያየት፣
በቅናሽ ዋጋ ፣
እቤትዎ ደረስ
በፓርኪንግ ሂሳብ
እንኳን ደስ አሎት የምንለው አሁን ነው
ቲቪ በማየት ብቻ ቤትዎ ሆነው በርካሽ ዋጋ ይገበያዩ
Frequency: 11545
Symbol rate : 45000
Polarization : Horizontal
Join Us on Ethiosat
የመርካቶ ቤተሰብን ይቀላቀሉ
https://t.me/MerkatoTv1
መርካቶ ቲቪ የእናንተ!!
እትዮጵያ ታምረት አፍሪካ ትሸምት!!
❤ 27👏 4🙏 2😁 1
Photo unavailableShow in Telegram
የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ላይ የአሰብ እና የቀይ ባሕር ጥያቄ ትክክል እንዳልሆነ "መቀላመድ"፤ "ባንዳነት" ነው አለ‼️
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ቅዳሜ መስከረም 17/2018 ዓ.ም. "ወደን እና ፈቅደን ስለምንሞትላት ኢትዮጵያችን ጠንቅቀን እናውቃለን" በሚል ርዕስ ባሰፈረውና በፌስቡክ ገጹ ላይ ባጋራው መልዕክት የቀይ ባሕር እና የአሰብ ጉዳይ ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ "የኢትዮጵያችን ሕመም ሆኖ የታላቅ አገርነቷን ክብር አሳንሷል። የጂኦ ፖለቲካ ብሔራዊ ወሳኝ ጥቅሟን ቀምቷል" ብሏል።
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ስለማረጋገጥ የሚያትተው የመከላከያ ሚኒስቴር መልዕክት "የኢትዮጵያ ወታደሮች የቀይ ባሕርን ጥያቄ በዓለም አደባባይ በይፋ መጠየቁ በታላቅ የደስታ ስሜት ሞልቶናል" ብሏል።
የመከላከያ ሚኒስቴር በይፋዊ የፌስ ቡክ ገፁ ላይ ባሰፈረው በዚህ መልዕክቱ ሠራዊቱ "ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም መረጋገጥ የትኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ለሰከንድ እንደማያቅማም" ገልጿል።
ጷግሜ 4፣2017 ዓ.ም. የተመረቀውን የሕዳሴውን ግድብ በመጥቀስ "የቀይ ባሕር ጉዳይም ዕውን የማይሆንበት ምክንያት እንደሌለ በጽኑ እናምናለን" በማለት አቋሙን አሳውቋል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
❤ 448👍 85😁 56👌 15🔥 8🤝 5👏 3
Photo unavailableShow in Telegram
መርካቶ ቲቪ ጀመረ!!
ቤትዎ ሆነው መገበያየት፣
በቅናሽ ዋጋ ፣
እቤትዎ ደረስ
በፓርኪንግ ሂሳብ
እንኳን ደስ አሎት የምንለው አሁን ነው
ቲቪ በማየት ብቻ ቤትዎ ሆነው በርካሽ ዋጋ ይገበያዩ
Frequency: 11545
Symbol rate : 45000
Polarization : Horizontal
Join Us on Ethiosat
የመርካቶ ቤተሰብን ይቀላቀሉ
https://t.me/MerkatoTv1
መርካቶ ቲቪ የእናንተ!!
እትዮጵያ ታምረት አፍሪካ ትሸምት!!
❤ 22
የጸጥታው ም/ቤት በኢራን ላይ በድጋሚ የጣለው ማዕቀብ…
አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ም/ቤት ከኒውክሌር ፕሮግራም ጋር በተያያዘ በኢራን ላይ በድጋሚ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ማዕቀብ ጥሏል፡፡
ምክር ቤቱ በፈረንጆቹ 2015 ስምምነት መሠረት በኢራን ላይ ተነስቶ የነበረው ማዕቀብ ነው በድጋሚ እንዲጣል የወሰነው፡፡
ውሳኔው የተላለፈውም ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ እና ጀርመን ኢራን ስምምነቱን ሙሉ ለሙሉ ለመተግበር ቁርጠኛ አይደለችም በሚል ቅሬታ ማቅረባቸውን ተከትሎ ነው፡፡
በአንጻሩ ቻይና እና ሩሲያ በኢራን ላይ የሚጣለው ማዕቀብ ለስድስት ወራት እንዲዘገይ መጠየቃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ይሁን እንጂ በኢራን ላይ ማዕቀብ ለመጣል የቀረበው የውሳኔ ሃሳብ በሌሎቹ የጸጥታው ም/ቤት አባላት አብላጫ ድምጽ ማግኘቱ ተገልጿል፡፡
የኢራን ፕሬዚዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ÷ በቴህራን ላይ በድጋሚ የተጣለው ዓለም አቀፍ ማዕቀብ ተቀባይነት የሌለው፣ ሕገ ወጥና ኢፍትሃዊ ነው ሲሉ አውግዘዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ ኢራን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ የማበልጸግ ፍላጎት እንደሌላትና በጉዳዩ ላይም አስፈላጊውን መረጃ ለመስጠት ቁርጠኛ መሆኗን አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ውሳኔውን ተከትሎ ኢራን በዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ እና ጀርመን የሚገኙ አምባሳደሮቿን ለምክክር መጥራቷ ተጠቅሷል፡፡
በቴህራን ላይ በድጋሚ የተጣለው ሁሉን አቀፍ ማዕቀብ ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተመላክቷል፡፡
@Esat_tv1
@Esat_tv1
❤ 189💔 19😡 19👍 13😁 8👏 5🕊 1
ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ትምህርት ቤቶችን በደንብ መመልከት እንጀምራለን በተማሪ ቁጥር ልክ መጻሕፍትን ገዝቶ ያላዳረሰ ት/ቤት ካለ የእውቅና ፈቃዱ ይሰረዛል‼️
🗣ትምህርት ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ትምህርት ቢሮ በከተማዋ የሚገኙ የግል ትምህርት ቤቶች በተማሪዎቻቸው ቁጥር ልክ መጻሕፍትን ገዝተው ማሰራጨት ካልቻሉ የእውቅና ፈቃዳቸው እስከመሰረዝ የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጿል።
የቢሮው ሃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ " በግል ትምህርት ቤቶች አልፎ አልፎ የሚታየው የመጻሕፍት እጥረት ከህትመት ጋር በተገናኘ ምክንያት እጥረት ኖሮ ሳይሆን ገዝተው ለተማሪዎቻቸው ማሰራጨትን እንደ ወጪ እና እንደ ድካም ስለሚያስቡት ነው " ብለዋል።
ሃላፊው ይህን ያሉት በአዲስ ቲቪ በተላለፈ " በጠረጴዛ " በተሰኘ ፕሮግራም ላይ በቀረቡበት ወቅት ነው።
" የመማሪያ መጻሕፍት በበቂ ሁኔታ ታትመዋል?በተለይ በግል ት/ት ቤቶች ለተወሰነ ጊዜ መጻሕፍት ሽያጭ ይከናወን እና አልቋል ይባላል ይህ ለምን ሆነ ? " የሚል ጥያቄ ለትምህርት ቢሮ ሃላፊው ቀርቦላቸው ነበር።
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ምን መለሱ ?
" በተለይ አዲሱ ስርአተ ትምህርት ተግባራዊ ከሆነ በኋላ በልዩ ሁኔታ ድጋፍ ተደርጎ ለተማሪዎቻችን አንድ ለአንድ እንዲደርስ ተደርጎ ህትመቱ በበቂ ሁኔታ ተሰራጭቷል።
የመጻሕፍት ህትመት እና ስርጭት ላይ ለመንግሥት ተማሪዎች መጻሕፍት በነጻ ይሰጣል ለግል ትምህርት ቤቶች በሪቮልቪንግ ፈንድ 250 ሚሊየን ተፈቅዶልን ይህንን ስራ እየሰራን እንገኛለን።
የግል ትምህርት ቤቶች ላይ ያለው ችግር ከተማሪዎች የመጽሐፍ ገንዘብ ሰብስበው ከትምህርት ቢሮ ስቶር ገዝተው ትምህርት ቤታቸው ማድረስ እና ማሰራጨት እንደ ትልቅ እዳ ነው የሚቆጥሩት ።
እንደከተማ ግን በቂ ህትመት ታትሞ ስቶራችን ሙሉ ነው ችግሩ ት/ቤቶች መጻሕፍቶቹን ከስቶር ወስደው ለተማሪዎች ማከፋል ላይ ነው ያለው።
በተለይ የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ፈቃድ የሚሰጠው አካል እሱ ስለሆነ መጻሕፍት በተማሪዎቻቸው ቁጥር ልክ ወስደው ለተማሪዎቻቸው ያላዳረሱ ትምህርት ቤቶች ካሉ እውቅና ፈቃዳቸው እንዲሰረዝ ተግባብተናል።
በቂ መጻሕፍት አለን በግል ት/ቤቶች እየተሰራጨ ነው አሁንም በስርጭት ላይ ነው የሚገኘው ችግሩ ያለው ትምህርት ቤቶች ላይ ነው እንደ ወጪ እንደ ድካም ስለሚያስቡት ነው።
ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ትምህርት ቤቶችን በደንብ መመልከት እንጀምራለን በተማሪ ቁጥር ልክ መጻሕፍትን ገዝቶ ያላዳረሰ ት/ቤት ካለ የእውቅና ፈቃዱ ይሰረዛል።
አንድም ተማሪ ያለ መጽሐፍ መማር የለበትም ይሄንን አንታገስም ይህም የእርምጃችን አንዱ አካል ይሆናል " ብለዋል።
©TikvahEthiopia
@Esat_tv1
@Esat_tv1
❤ 184👍 18🔥 11😁 6💔 6👏 3👌 3
Photo unavailableShow in Telegram
መርካቶ ቲቪ ጀመረ!!
ቤትዎ ሆነው መገበያየት፣
በቅናሽ ዋጋ ፣
እቤትዎ ደረስ
በፓርኪንግ ሂሳብ
እንኳን ደስ አሎት የምንለው አሁን ነው
ቲቪ በማየት ብቻ ቤትዎ ሆነው በርካሽ ዋጋ ይገበያዩ
Frequency: 11545
Symbol rate : 45000
Polarization : Horizontal
Join Us on Ethiosat
የመርካቶ ቤተሰብን ይቀላቀሉ
https://t.me/MerkatoTv1
መርካቶ ቲቪ የእናንተ!!
እትዮጵያ ታምረት አፍሪካ ትሸምት!!
❤ 47😁 3👏 1
❤ 134👍 43🙏 24😁 12😭 6😡 2🕊 1
Photo unavailableShow in Telegram
ነገ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ‼️
ነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ ከሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ጋር በተያያዘ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ይፋ አደርጓል።
በዚህም መሠረት ፦
ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣
ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣
ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣
ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣
ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣
ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣
ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣
ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣
ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣
ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣
ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ መንገድ ይዘጋል።
አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ተላልፏል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
❤ 183👍 29😁 7😡 4👏 2😱 1
Photo unavailableShow in Telegram
አንቶኒዮ ጉተሬዝ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ በመመረቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ‼️
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸውም ሁለቱ ወገኖች በቀጣናው ብሎም በዓለም አቀፍ የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። አንቶኒዮ ጉተሬዝ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ በመመረቁ ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
በተጨማሪም በቅርቡ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ጉባዔን በስኬት ማስተናገዷን አስታውሰው፥ ለዚህም የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
❤ 201👏 24👍 14🙏 6👌 5😁 2
Photo unavailableShow in Telegram
የ12ኛ ክፍል ማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች እስከ መስከረም 14 ድረስ የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን ማስተካከል እንደሚችሉ ተገለጸ!‼️
በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደው የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች እስከ መስከረም 14 ድረስ የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን ማስተካከል እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት አምጥተው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከተጠቀሰው ቀን ድረስ ማስተካከል የሚችሉ መሆኑን ነው የገለጸው።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን እንደሚቀበል የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ ተማሪዎች ምርጫቸው ውስጥ ማካተት የሚችሉ መሆኑን አስታውቋል።እንዲሁም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምርጫ ውስጥ የማይካተቱ መሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
Photo unavailableShow in Telegram
👉 አስደሳች ዜና!!
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው አያት-ካዛንቺስ መንደር ሽያጭ ጀመረ ::
👉እጅግ ውብ ዕይታዎች ያሉት
እንደፍላጎትዎ ....
ከ ባለ 1 እስከ ባለ 4 መኝታ (45-160ካሬ)
👉ቅድመ ክፍያ 10% ብቻ ከ 477,500 ብር ጀምሮ መያዝ ይችላሉ ::
👉 አስበልጦ ለሚከፍሉ 25% ቅናሽ ተዘጋጅቷል ::
👉በግቢው ውስጥ
➤ ት/ቤት እና የጤና ማዕከል
➤ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ መጫወቻ
➤ መዋኛ ገንዳ
➤ የሳይክል እና የእግር ሽርሽር ስፍራዎች
➤ ሰፊ የመኪና መቆሚያ ከ7/24 ጥበቃ ጋር
➤ የመኪና ቻርጀር ስፍራዎች
👉ቀድሞ ለመጣ ቅድሚያ ይስተናገዳል!
✅ እንዲሁም ግንባታቸው ከ90% በላይ የተጠናቀቁ ቤቶች በ15% ቅድመ ክፍያ ብቻ።
✅በተጨማሪ አክሲዎን ከ50% በላይ ትርፍ ያለውን ሸር ከ112,500 ብር ጀምሮ ያገኛሉ።
✅የንግድ ሱቆችም በተለያዩ የካሬ አማራጮች ከ20-500ካሬ ያገኛሉ።
📞 ለበለጠ መረጃ 7/24 በ0928579029
ይደውሉልን !!!
❤ 21👏 2
Photo unavailableShow in Telegram
የህዳሴ ግድብ ለጎብኚዎች ክፍት መደረጉ ተገለፀ‼️
በቡድን 50 50 በመሆን መጎብኘት ይቻላል ተብሏል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር ይህ አገልግሎት መጀመሩን ይፋ አድርጓል።
የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፤ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር አገልግሎቱ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ቦታውን መጎብኘት የሚፈልጉ አካላት፣ ተቋማት ካሉ ስፍራውን ለመጎብኘት ስራዎች መጀመራቸውን አንስተዋል።
በሳምንት 2 በረራ የሚኖር ሲሆን፤ በቡድን 50 50 በመሆን መጎብኘት ይቻላል ተብሏል።
የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጠናቋል ያሉት ሚኒስትሯ፤ ከሰኞ ጀምሮ ምዝገባ ይካሄዳል ብለዋል።
አሁን ላይ አገልግሎቱ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር መጀመሩን አንስተው ፤ በቀጣይ ከተመዘገቡ እና ፍቃድ ካላቸው አስጎብኚ ድርጅቶች ጋር ለመስራት በዕቅድ ተይዞ እየተሰራበት መሆኑን አንስተዋል።
ስፍራው አሁንም ግንባታ ላይ በመሆኑ ጉብኝቱ ደርሶ መልስ እንደሚሆን ገልጸዋል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
❤ 284👍 52👏 21😁 21🕊 11🔥 2😭 2
Photo unavailableShow in Telegram
👉 አስደሳች ዜና!!
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው አያት-ካዛንቺስ መንደር ሽያጭ ጀመረ ::
👉እጅግ ውብ ዕይታዎች ያሉት
እንደፍላጎትዎ ....
ከ ባለ 1 እስከ ባለ 4 መኝታ (45-160ካሬ)
👉ቅድመ ክፍያ 10% ብቻ ከ 477,500 ብር ጀምሮ መያዝ ይችላሉ ::
👉 አስበልጦ ለሚከፍሉ 25% ቅናሽ ተዘጋጅቷል ::
👉በግቢው ውስጥ
➤ ት/ቤት እና የጤና ማዕከል
➤ እግር ኳስና ቅርጫት ኳስ መጫወቻ
➤ መዋኛ ገንዳ
➤ የሳይክል እና የእግር ሽርሽር ስፍራዎች
➤ ሰፊ የመኪና መቆሚያ ከ7/24 ጥበቃ ጋር
➤ የመኪና ቻርጀር ስፍራዎች
👉ቀድሞ ለመጣ ቅድሚያ ይስተናገዳል!
✅ እንዲሁም ግንባታቸው ከ90% በላይ የተጠናቀቁ ቤቶች በ15% ቅድመ ክፍያ ብቻ።
✅በተጨማሪ አክሲዎን ከ50% በላይ ትርፍ ያለውን ሸር ከ112,500 ብር ጀምሮ ያገኛሉ።
✅የንግድ ሱቆችም በተለያዩ የካሬ አማራጮች ከ20-500ካሬ ያገኛሉ።
📞 ለበለጠ መረጃ 7/24 በ0928579029
ይደውሉልን !!!
❤ 47
إظهار الكل...
❤ 158😡 25👍 15🔥 1😁 1
