ar
Feedback
ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

الذهاب إلى القناة على Telegram

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

إظهار المزيد
2025 عام في الأرقامsnowflakes fon
card fon
44 133
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
-21530 أيام
أرشيف المشاركات
እስራኤል ከሳዑዲ ጋር መደበኛ ግንኙነት ብትጀምር እንኳን ፍልስጤም የምትባል ሀገር መመስረቷን እንደማትቀበል ኔታንያሁ ተናገሩ የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የፍልስጤም መንግስት ምስረታ ላይ ያላቸውን ጠንካራ ተቃውሞ በድጋሚ ገልጸዋል፣ እስራኤል በጉዳዩ ላይ ከሳዑዲ አረቢያ ጋር መደበኛ ግንኙነት ብትመሰርት እንኳን ይህንን አቋሟን አትቀይርም ብለዋል። ከእስራኤል የዜና አውታር አቡ አሊ ኤክስፕረስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ስለ ተስፋው ተጠይቀው፣ ኔታንያሁ “የፍልስጤም መንግስት አይኖርም። የዚያን ያህል ቀላል አይደለም፤ ይህ ለእስራኤል ህልውና ስጋት ነው" ብለዋል።ሆኖም የእስራኤሉ መሪ የጋዛ ጦርነት ማብቃቱን በማንሳት ከሳዑዲ አረቢያ ጋር መደበኛ ግንኙነትን መመስረት በተመለከተ አሁንም "ጥንቃቄ የሚፈልግ ብሩህ ተስፋ" እንዳላቸው ተናግረዋል ። "ሁኔታዎች ሊኖሩ ይችላሉ ፤ ነገር ግን ሁኔታዎቹ በሁለቱም ወገኖች ተቀባይነት ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ደግሞም ለሁለቱም ወገኖች ጥሩ ነው" ብለዋል፡፡ "አንድ ላይ ከሆንን  በጣም ጥሩ በመሆኑ አስፈላጊ ጥቅሞቻችንን እንጠብቃለን" ሲሉ አክለዋል፡፡በሌላ በኩል ሃማስ እስራኤልን በጋዛ ቢጫ መስመር ተብሎ የሚጠራውን የእርቅ ማካለሉን ቀይራለች ፤ አዲስ ነዋሪዎችን ማፈናቀል ዘመቻ በማድረግ የተኩስ አቁምን እንደጣሰች ከሷል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች “የተኩስ አቁም ደካማነት” ስጋት እንዳሳደረባቸው እና በጋዛ የፍልስጤማውያን ግድያ “መቆም አለበት” ብለዋል። የሂዩማን ራይትስ ዎች ሪፖርት በበኩሉ የእስራኤል ጦር በያዘው ዌስት ባንክ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያንን ማፈናቀሉ የጦር ወንጀክ እና በሰው ልጆች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች መኖሩን ያሳያል ብሏል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
👎 78 18👍 5
Photo unavailableShow in Telegram
5👎 4🤯 2
150 የሺሻ ማጨሻ ዕቃዎችን ማቃጠሉን የደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ አስታወቀ ለወንጀል መንስኤ የሆነዉን ሺሻ የማስጨስ ተግባርን ለማስቀረት ጥብቅ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑ የደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ አስታዉቋል፡፡ በከተማዋ ዘላቂ ሰላምና አስተማማኝ ፀጥታ ለማስፈን ለወንጀል መንስኤ የሆኑ ተግባራትን በመለየት ህጋዊ እርምጃ እየወሰድኩ ነዉ ሲል ለተግባራዊነቱ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጿል። ‎ ‎በህገወጥ ንግድ ከተሰማሩ ሺሻ ማጨሻ ቤቶች በህግ አግባብ የተሰበሰበ 150 የሺሻ ማጨሻ ዕቃዎችን በቃጠሎ እንዲወገድ መደረጉ የደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ የወንጀል መከላከል ምክትል መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዋና ክፍል  የኦፕሬሸን ክፍል ሃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር አወል ይማም ገልፀዋል። ‎ ከተማዋ ለነዋሪዉ ሆነ ለእንግዶችዋ ሰላማዊና ምቹ የመኖሪያ አካባቢ ትሆን ዘንድ ህገወጥነትን በማጋለጥና በመከላከል የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ለማስቻል ከዚህ ቀደም ነዋሪው ህዝብ ከፖሊስ ጎን በመሆን የሚያደርገው እገዛና ተደጋግፎ መስራትን አጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል መካሉን ብስራት ከደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ያገኘው መረጃ ያሳያል:: #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
18👌 9😁 6👍 2😢 1
4
Photo unavailableShow in Telegram
በኢትዮጵያ ዛሬም ተጨማሪ ሁለት ሰዎች የማርበርግ ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
13🙏 6🤔 2
ዜሌንስኪ የዩክሬን ጦርነትን ለማስቆም ከአሜሪካ ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸዉን ተናገሩ የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ከሩሲያ ጋር ያለውን ጦርነት ለማስቆም ከአሜሪካ ጋር በ"ራዕያቸው" ላይ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል ።በሰፊው ይፋ በሆነው እቅድ ኪየቭ አሁንም የምትቆጣጠራቸውን የዩክሬን የዶኔትስክ ግዛት ጉልህ ስፍራዎችን አሳልፋ ለሩሲያ ትሰጣለች፣ የሰራዊቷን መጠን ትቀንሳለች እንዲሁም ኔቶን ወይም የሰሜን አትልንቲክ ጦር ቃልኪዳን ላለመቀላቀል ቃል ትገባለች የሚለዉን ትቀበላለች፡፡ ቀደም ሲል ዩክሬን ይህንኑ ነጥቦች ውድቅ አድርጋዋለች። የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ እና የሩሲያው አቻቸው ኪሪል ዲሚትሪየቭ ያደረጉትን ስብሰባ ተከትሎ ብቅ ያለውን እቅድ በማዘጋጀት ላይ ዩክሬን አልተሳተፈችም የሚለውን ዉንጀላ ዋይት ሀውስ ዉድቅ አድርጋለች።በረቂቅ እቅዱ ውስጥ የተካተቱት ድንጋጌዎች ከኪየቭ በጥንቃቄ ዲፕሎማሲያዊ ምላሽ አግኝተዋል።እ.ኤ.አ. የካቲት 2022 የሩሲያ አጠቃላይ ወረራ ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ ዩክሬን በአሜሪካ ወታደራዊ ድጋፍ ላይ በከፍተኛ ደረጃ ትተማመን ነበር፣ ነገር ግን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካን አቋም በመቀየር ተጨማሪ ርዳታ በኔቶ አጋሮቻቸው እንዲደረግ እና የሰላም ስምምነትን ማስፈን ቀዳሚ ተግባር ሆኗል። ረቂቁ የዊትኮፍ-ዲሚትሪቭ እቅድ የወጣው ሩሲያ በምስራቃዊ ዩክሬን አነስተኛ የግዛት ጥቅሞች እንዳገኘች ስትናገር በዚህ በኩል ደግሞ ዘሌንስኪ በሀገር ውስጥ ችግር ከፍተኛ ባለስልጣናትን በ100ሚ ዶላር የሙስና ቅሌት ውስጥ በገቡበት ወቅት ነዉ።የዩክሬን መሪ በምሽት ንግግራቸው በኪየቭ የሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ ባለስልጣናት “ያቀረቡትን ሃሳብ፣ ጦርነቱን ለማቆም የዕቅዱን ነጥቦች ” አቅርበዋል ብለዋል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
10👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
በከባድ የውንብድና ተግባር የተከሰሱ ግለሰቦች እስከ 16 አመት እስራት እንደተፈረደባቸው ተገለፀ በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ አስተዳደር በከባድ የውንብድና ተግባራት የተከሰሱ ግለሰቦች እስከ 16 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እና በገንዘብ እንዲቀጡ የስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ ማስተላለፉን የስልጤ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።ተከሳሾቹ እነ አብድሽኩር ሙባሪክ ኑርሰቦ በተባሉ መዝገብ የተከሰሱና አድራሻቸው ወራቤ ከተማ አሰተዳደር የሆኑ 18 ግለሰቦች መሆናቸውን በውሳኔ መዝገቡ ላይ ተገልጿል። በተለያዩ የወራቤ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ላይ ሀይልና ማስፈራራትን በመጠቀምና በመደብደብ የተለያዩ ሞባይሎችን አስገደዉ ወስደዋል፡፡በተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ንብረት ያወደሙና የፌድራል መንገድን በህብረት በመሆን በመዝጋት እንዲሁም የፖሊስ አባላትን ጨምሮ በርካታ ነዋሪዎችን በተለያያ ሰዓት በቡድን በመሆን የደበደቡ በመሆኑ በፈጸሟቸው ከባባድ የውንብድና ተግባራት ክስ በመመስረት ለውሳኔ መብቃቱን መግለጫው ያመላክታል። በዚህም ግለሰቦቹ በቡድንና በተናጠል በወራቤ ከተማ ልዩ ልዩ ሰፈሮች በመዟዟር ከታህሳስ 2015 ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 2016 በተለያዩ ጊዜያት ከተለያዩ የግል ተባዳዮች ከዘመናዊ ሞባይል ዝርፊያ እስከ እስከ ንብረት ማውደምና ድብደባ፣ የጸጥታ አካላትን ከመደብደብ የተለያዩ ግለሰቦች ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ የዘለቀ ተደጋጋሚ የውንብድና ተግባራት መፈጸማቸውን የሚያትቱ 22 ክሶች መመስረታቸውን በውሳኔ ዝርዝር ላይ ተመላክቷል፡፡ የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ አቃቤ ህግ ከፖሊስ ተጣርቶ በቀረበለት መረጃ መሰረት የመሰረተውን ክስ ሲመለከት የቆየው የስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህዳር 11 ቀን 2018 በዋለው ችሎት ከ18 ተከሳሾች ውስጥ 3ቱ በነጻ ሲሰናበቱ 8ቱ በ2 አመት የገደብ ቅጣት፣  7 ተከሳሾች በጽኑ እስራት እንዲቀጡ መወሰኑን ከስልጤ ፖሊስ መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
15🤔 5👍 2👏 1
በከባድ የውንብድና ተግባር የተከሰሱ ግለሰቦች እስከ 16 አመት እስራት እንደተፈረደባቸው ተገለፀ በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ አስተዳደር በከባድ የውንብድና ተግባራት የተከሰሱ ግለሰቦች እስከ 16 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እና በገንዘብ እንዲቀጡ የስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ ማስተላለፉን የስልጤ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።ተከሳሾቹ እነ አብድሽኩር ሙባሪክ ኑርሰቦ በተባሉ መዝገብ የተከሰሱና አድራሻቸው ወራቤ ከተማ አሰተዳደር የሆኑ 18 ግለሰቦች መሆናቸውን በውሳኔ መዝገቡ ላይ ተገልጿል። በተለያዩ የወራቤ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ላይ ሀይልና ማስፈራራትን በመጠቀምና በመደብደብ የተለያዩ ሞባይሎችን አስገደዉ ወስደዋል፡፡በተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ ንብረት ያወደሙና የፌድራል መንገድን በህብረት በመሆን በመዝጋት እንዲሁም የፖሊስ አባላትን ጨምሮ በርካታ ነዋሪዎችን በተለያያ ሰዓት በቡድን በመሆን የደበደቡ በመሆኑ በፈጸሟቸው ከባባድ የውንብድና ተግባራት ክስ በመመስረት ለውሳኔ መብቃቱን መግለጫው ያመላክታል። በዚህም ግለሰቦቹ በቡድንና በተናጠል በወራቤ ከተማ ልዩ ልዩ ሰፈሮች በመዟዟር ከታህሳስ 2015 ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 2016 በተለያዩ ጊዜያት ከተለያዩ የግል ተባዳዮች ከዘመናዊ ሞባይል ዝርፊያ እስከ እስከ ንብረት ማውደምና ድብደባ፣ የጸጥታ አካላትን ከመደብደብ የተለያዩ ግለሰቦች ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ የዘለቀ ተደጋጋሚ የውንብድና ተግባራት መፈጸማቸውን የሚያትቱ 22 ክሶች መመስረታቸውን በውሳኔ ዝርዝር ላይ ተመላክቷል፡፡ የስልጤ ዞን ፍትህ መምሪያ አቃቤ ህግ ከፖሊስ ተጣርቶ በቀረበለት መረጃ መሰረት የመሰረተውን ክስ ሲመለከት የቆየው የስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህዳር 11 ቀን 2018 በዋለው ችሎት ከ18 ተከሳሾች ውስጥ 3ቱ በነጻ ሲሰናበቱ 8ቱ በ2 አመት የገደብ ቅጣት፣  7 ተከሳሾች በጽኑ እስራት እንዲቀጡ መወሰኑን ከስልጤ ፖሊስ መምሪያ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
የማርበርግ ቫይረስ በወንድ የዘር ፈሳሽ ውስጥ ለአንድ አመት ይቆያል አንድ ማርበርግ የተያዘ ሰው ከተያዘበት 2ኛ ቀን ጀምሮ አስከ 21 ቀን ባለው ግዜ ውስጥ ምልክት የሚያሳይ ሲሆን በተመሳሳይም ወደሌላ ሰውም  ያስተላልፍል። በቫይረስ የሚከሰተው ማርበርግ ከ24 አስከ 88 በመቶ የሞት ምጣኔ እንዳለው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። የጤና ሚኒስቴር በማርበርግ በሽታ ዙሪያ በዛሬው እለት ለሚዲያ ባለሙያዎች ስለበሽታው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጥቷል።በግንዛቤ ማስጨበጫውም ይህ በቫይረስ የሚከሰተው የማርበርገር ቫይረስ የተያዘ ወንድ ሰው ቢሻለውም በዘር ፈሳሹ ውስጥ ለአንድ አመት ስለሚቆን ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የድንገተኛ ክፍል ዶክተር ወልደሰንበት ዋጋነው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። የበሽታው ምልክቶች በአብዛኛው ከ2 እስከ 21 ቀናት ባለው ጊዜ ውስጥ እንደሚታዩ የገለፁት ዶክተር ወልደሰንበት በቫይረሱ የተያዘ ሰው በመጀመሪያዉ ደረጃ ላይ ከፍተኛ ትኩሳት፣ ከባድ ራስ ምታት፣ ከባድ የጡንቻና የመገጣጠሚያ ህመም፣ ድካም ስሜት እንደሚሰማው ተናግረዋል።ከጥቂት ቀናት በኋላ ከባድ ተቅማጥ፣ የሆድ ቁርጠት፣ ማቅለሽለሽ፣ ማስታወክ፣ የደረት እና የጉሮሮ ህመም ስሜቶች የሚሰማ ሲሆን ከ5 እስከ 7 ቀናት  ከባድ የደም መፍሰስ ከአፍንጫ፣ ከድድ፣ ከዓይን እና የቆዳ ስር፣ የጉበት እና የኩላሊት ድካም፣ የንቃተ ህሊና መሳት፣ የብዝሃ-አካል ስራ መቆም  እና ሞት ያስከትላል ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪ  የዓይን መቅላት፣ የቆዳ ሽፍታ በተለይ በደረት፣ ጀርባና ሆድ አካባቢ ህመም የሚኖር ይሆናል።ለጊዜው ቫይረሱን የሚያጠፋ የተረጋገጠ ቀጥተኛ መድኃኒት ወይም ክትባት አለመኖሩን የተናገሩት ዶክተር ወልደሰንበት በምርምር ላይ ያሉ የህክምና እና የክትባት አይነቶች እንዳሉ አስረድተዋል። በህክምና ተቋማት ህክምና  የሚሰጠው ህክምና ምልክቶችን ለማስታገስ መሆኑም ተነግራል ፈሳሽ መተካት  በከፍተኛ ተቅማጥ እና ማስታወክ የጠፋውን ፈሳሽ መሙላት ያስፈልጋል ተብሏል፤የደም መፍሰስ ቁጥጥር: የደም ግፊትን ማረጋጋት እና የደም መርጋት መከላከል ማከም ያስፈልጋል ተብሏል። የጤና ባለሙያዎች የታመሙ ሰዎችን ሲያክሙ ጓንት፣ ጋውን፣ ጭንብል እና የዓይን መከላከያ የግድ መጠቀም አለባቸው የተባለ ሳሆን ንጽህና እጅን በአግባቡ በሳሙና መታጠብ ይገባል ተብሏል። በትላንትናው እለት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በማህበራዊ ትስስር ገፆቸው የ ዕለት የማርበርግ መረጃ ባወጡት መሰረት 2 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ መሆኑን የገለፁ ሲሆን በእለቱም 5 የላብራቶሪ ምርመራዎች የተካሄደ ሲሆን፥ 2 ሰው በቫይረሱ መያዙንና 3 ሰዎች ደግሞ ነጻ መሆናቸው ተገልጿል።በሽታው መከሰቱ ከተገለጸበት ቀን አንስቶ እስካሁን 33 የላብራቶሪ ምርመራዎች የተደረገ ሲሆን ቫይረሱ በ6 ሰዎች ላይ መገኘቱ በላብራቶሪ ተረጋግጧል። በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
😱 18 13😁 6👎 1🤔 1🙏 1
Photo unavailableShow in Telegram
በእስራኤል የአሜሪካ አምባሳደር ከተከሰሱ ሰላይ ጋር መገናኘታቸዉን ዋይት ሀውስ እንደማያዉቅ ተሰማ ዋይት ሀውስ በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ በእስራኤል የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ሁካቢ እና የቀድሞ የአሜሪካ ባህር ሃይል መኮንን ጆናታን ፖላርድ ለእስራኤል በመሰለል ተከሶ ለአስርት አመታት በእስር ላይ የቆየዉ ግለሰብ ጋር ንግግር እንደነበረ አለማወቁን አስታዉቋል፡፡ የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሌቪት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት የትራምፕ አስተዳደር ስለ ዉይይቱ ምንም ዓይነት ቅድመ መረጃ እንደሌላቸዉና አምባሳደሩ ማይክ ሃካቢ ለዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል እየሰሩ ነዉ ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ውይይቱ በሃካቢ ይፋዊ የጊዜ ሰሌዳ ላይ እንዳልነበረ እና የአሜሪካ የስለላ ኤጀንሲዎች ሳያውቁት መደረጉን ዘ ታይምስ ስማቸውን ያልተጠቀሳቸዉን ሁለት የአሜሪካ ባለስልጣናትን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡ የቀድሞ የዩናይትድ ስቴትስ የባህር ሃይል መረጃ ተንታኝ ፖላርድ በሺዎች የሚቆጠሩ በጣም ሚስጥራዊ የሆኑ የአሜሪካ መረጃዎችን ለገንዘብ እና ለስጦታ በሚል በመስጠቱ ለፍርድ ቀርቦ በእድሜ ልክ እስራት ተወስኖበታል፡፡ ይህም አንድ ሰው አጋር ሀገርን ለመሰለል ከተሰጣለበት እስር ሁሉ የከፋው ቅጣት ነው፡፡ ፖላርድ ለ30 ዓመታት ያህል በእስር ቆይቷል፡፡ በ2020 ወደ እስራኤል ከተዘዋወረ በኃላ በእስራኤል ውስጥ አንዳንድ ሰዎች እንደ ጀግና ይቆጠሩታል።ጉዳዩ በወቅቱ የአሜሪካን እና የእስራኤልን ግንኙነት ክፉኛ ያበላሸው ሲሆን አሁንም በአሜሪካ ታሪክ ውስጥ በጣም ጎጂ ከሆኑ ሚስጥራዊ መረጃዎች አንዱ ተደርጎ ይወሰዳል።ሐሙስ ዕለት የእስራኤሉ አይ 24 የዜና አውታር እንደዘገበዉ ፖላርድ ከአምባሳደር ሃካቢ ጋር የተደረገው ስብሰባ የተካሄደው በእኔ ጥያቄ ነው ብሏል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
14😁 6
Photo unavailableShow in Telegram
Photo unavailableShow in Telegram
በኢትዮጵያ 80 በመቶ የሚሆኑት ህፃናት ዘግይተው ወደ ህክምና ተቋም የሚመጡ በመሆናቸው ለከፋ የስኳር ህመም ተጋላጭ እየሆኑ ነው በኢትዮጵያ በዓይነት ሁለት የስኳር ሕመም ወይም “ታይፕ ቱ ዲያቤትስ” የሚጠቁ ሕጻናት ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የኢትዮጵያ የስኳር ሕመምተኞች ማህበር አስታውቋል። የህፃናት ሆርሞንና የስኳር ሀኪም ዶክተር ሰዋገኝ የሺዋስ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት በማህበረሰቡ ዘንድ ስለ ስኳር በሽታ ያለው ግንዛቤ አናሳ በመሆኑ  በርካታ ህፃናት ወደ ህክምና ተቋም የሚመጡት ህመሙ ከተባባሰባቸው በኋላ ነው። በተለያዩ ሆስፒታሎች በተደረገው ጥናት መሰረት 80 በመቶ የሚደርሱ ህፃናት ለከፋ ህመም ከተጋለጡና ህመሙ መጨረሻ ደረጃ ላይ ሲደርስ ህፃናቱ ወደ ጤና ተቋማት እንደሚመጡ ያሳያል።አሁን ላይ በስኳር ህመም እየተጠቁ ያሉ ህፃናት ቁጥር በእጅጉን እየጨመረ መምጣቱን የህክምና ባለሙያው  ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ስኳር ህመምተኞች ስር የታቀፋ 20 ሺህ ህፃናት መኖራቸውን ገልፀው በኢትዮጵያ በስኳር ህመም የተጠቁ ህፃናት ቁጥር ግን ከዚህም ሊበልጥ ይችላል። ዶክተር ሰዋገኝ አክለውም  በህፃናት የስኳር ህክምና አሰጣጥ ዙሪያም ሊቀረፋ የሚገባቸው ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል። በበቂ ሁኔታ የላብራቶሪ ግብአት አለመሟላት፣ የህክምና ባለሙያዎች ቁጥር ማነስ ከእነዚህ መካከል ይገኙበታል የተባለ ሲሆን የስነልቦና ድጋፍን ያካተተ ህክምናን ጭምር መስጠት እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል። በቅድስት ደጀኔ #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
16😢 5💔 2👎 1🙏 1
አዳዲስ የማይክሮ ፋይናንስ አገልግሎቶችን ይዞ የመጣው ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር በይፋ ስራ ጀመረ 👉 ለሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች በቀላሉ የፋይናንስ ድጋፍ የሚያገኙበት አማራጭ መያዙንም ገልጿል። በህብረት ስራ ማህበር አዋጅ ቁጥር 985/09 በ2017 ዓ.ም በህጋዊ መንገድ የተቋቋመው ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር በሴት የቦርድ አባላት የሚመራና በዘርፉ የረጅም ዓመት ልምድ ባካበቱ ባለሞያዎች የተቋቋመ መሆኑ ተነግሯል። በዘርፉ አሁን ላይ እየተተገበሩ ከሚገኙ የብድር አገልግሎቶች በተለየ መልኩ አዳዲስ አሰራሮችን ይዞ መምጣቱን በመጠቆም ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚነትን ታሳቢ ያደረገ ስለመሆኑም ተመላክቷል። በቡድን የሚመጡ ብድር ፈላጊዎች ልዩ የወለድ ቅናሽ እንዲያገኙ የሚያስችል አሰራር ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ በማድረግ ስራውን የሚጀምረው ኦሜጋ ወላጆች ለታዳጊ ተማሪ ልጆቻቸው የት/ቤት ክፍያ ብድር እንዲያገኙ እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከትምህርታቸው ጋር በተገናኘ የሚያስፈልጋቸውን ብድር ለመስጠት መዘጋጀቱን ጠቁሟል። ለጤና አገልግሎት የሚውል ብሎም ለተለያዩ የውጭ ጉዞዎች የሚሆን ብድር ማህበሩ በልዩነት ይዟቸው ከመጡ ብድሮች መካከል ይጠቀሳሉ። ብድር ፈላጊዎች የአጭር ጊዜ አነስተኛ ወለድ ያለው ብድር የሚያገኙ ሲሆን ከወለድ ነፃ ብድር በማመቻቸት የተቀላጠፈ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ተዘጋጅቻለሁም ብሏል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የሚዲያ እና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ከሚሰሯቸው ስራዎች ጋር በተገናኘ የፋይናንስ ችግር ለስራቸው እንቅፋት እንዳይሆን ልዩ የብድር አገልግሎት ለመስጠት መዘጋጀቱን ማህበሩ ይፋ አድርጓል። ይህንንም ተግባራዊ ማድረግ የሚያስችል ስምምነት የኪነ ጥበብና የሚዲያ ባለሙያዎች ከኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ጋር በዛሬው ዕለት ተፈራርመዋል። #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
12👎 1
1
Photo unavailableShow in Telegram
ቤጂንግ ቻይናውያን በመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ የማዕድን ባሪያዎች የመሆን ስጋት እንዳላቸው አስጠነቀቀች በመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ የሚገኘው የቤጂንግ ኤምባሲ የቻይና ዜጎች እንደ ወርቅ ማዕድን ባሉ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ እንዳይሰሩ አስጠንቅቋል ፣ “የማዕድን ባሪያዎች” ሊሆኑ ይችላሉ ሲል ስጋቱን አክሏል።ኤምባሲው በሰጠዉ መግለጫ እንዳስታወቀው ባለፉት አመታት በወርቅ ማዕድን ስራ ላይ የተሰማሩ የቻይና ዜጎች "የፀጥታ ችግር አጋጥሟቸዋል ወይም ከፍተኛ የደህንነት ስጋት አጋጥሟቸዋል" ብሏል። አንዳንዶች ከፍተኛ ንዋይ በማፍሰስ የገንዘብ ኪሳራ ሲደርስባቸው፣ ሌሎች ደግሞ አካላዊ ማስፈራሪያ ደርሶባቸዋል፣ የአንዳንድ ዜጎች ሰነዶች ተወርሰው “የማዕድን ስራዎች ባሪያዎች” እንዲሆኑ መደረጉን ገልጿል።"የተወሰኑት በጸረ-መንግስት ታጣቂዎች ጥቃት ደርሶባቸው ተገድለዋል፣ሌሎች ደግሞ በተለያዩ ሀይሎች እና ሀገራት መካከል በተደረጉ ግጭቶች የተያዙ እና የተወሰኑት አደገኛ በሆኑ እንደ ወባ ባሉ ገዳይ በሽታዎች ሞተዋል" ሲል መግለጫው ገልጿል። ከሌሎች ባለአክሲዮኖች ጋር በተፈጠረ አለመግባባት የተከሰቱት በ‹መኪና ግጭት› ወይም ‹‹ስቅላት›› የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ወይም ተገድለዋል ሲልም አስጠንቅቋል።"ከመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ውጭ ወደሚገኙ ቀይ ዞኖች ለስራ እንዳትጓዙ እና ከፍተኛ ስጋት ያለባቸውን እንደ ወርቅ ማዕድን ያሉ ኢንዱስትሪዎች እንዳትሳተፉ" ያለው ኤምባሲው ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በአስቸኳይ እንዲያቆሙ፣ አካባቢውን ለቀው ለኤምባሲው እንዲያመለክቱ አሳስቧል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
11
ቫሴክቶሚ  ልጅ መውለድ ለማይፈልጉ ወንዶች  ውጤታማ የእርግዝና መከላከያ አማራጭ ቢሆንም በኢትዮጵያ የተጠቃሚ ወንዶች ቁጥር አነስተኛ ነው ተባለ። በዛሬዉ እለት የዓለም ቫሴክቶሚ ቀን እየታሰበ ይገኛል፡፡የዓለም የቫሴክቶሚ ቀን በኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ በአርባ ምንጭ ከተማ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ሴንት ፓል ኢንስቲትዩት ፎር ሪፕሮዳክቲቭ ሄልዝ ኤንድ ራይትስ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣ ከማሪ ስቶፕስ ኢትዮጵያ እና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር  ተዘጋጅቷል። በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒቲል የቤተሰብ ዕቅድ እና ስነ ተዋልዶ ሰብ ስፔሺሊስት ዶ/ር ዘሪሁን በየነ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ቫሴክቶሚ ማለት የወንድ ዘር ማሰትላለፊያ ቱቦ በመቋጠር የሚሰራ ዘላቂ እና ቋሚ የሆነ የእርግዝና  መከላከያ ዘዴ ነው።የዚህ አመት መሪ ቃል ሲሆን በቤተሰብ እቅድ ውስጥ የጋራ ሃላፊነት አስፈላጊነት እና በሥነ ተዋልዶ ጤና ውስጥ የወንዶች ተሳትፎ አስፈላጊነት ያጎላል።  ቫሴክቶሚ ወደፊት ልጅ መውለድ እንደማይፈልጉ እርግጠኛ ለሆኑ ጥንዶች ተስማሚ  ውጤታማ  የእርግዝና መከላከያ አማራጭ ዘዴ መሆኑን ዶክተር ዘሪሁን  አስረድተዋል ።ምንም እንኳን የተረጋገጠ ጠቀሜታዎች ቢኖሩትም በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ ዝቅተኛ እና መካከለኛ ሀገራት እንዲሁም  በኢትዮጲያ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማህበረሰብ  ቁጥር ውስን መሆኑ በዚህ ወቅት ተገልጿል። ወንዶች ይህን የእርግዝና መከላከያ ዘዴን መጠቀም ቢችሉ በስነተዋልዶ ጤና  እና በቤተሰብ እቅድ ላይ ንቁ  ተሳትፎ እንዲያደርጉ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ሲሉ ዶክተር ዘሪሁን ገልፀው ይህም ጤናማ እና የተሻለ የቤተሰብ ህይወትን ለመምራት አስተዋጾ እንዳለው ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል። ቅድስት ደጀኔ #ዳጉ_ጆርናል
إظهار الكل...
👎 56 13🤔 3😁 1
Photo unavailableShow in Telegram