ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
Ir al canal en Telegram
በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
Mostrar más2025 año en números

50 484
Suscriptores
-624 horas
+27 días
+10030 días
Archivo de publicaciones
Photo unavailableShow in Telegram
"ባርከኒ አባ እንሣእ በረከተከ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሳሙኤል አባ ባርከኒ እንሣእ በረከተከ።"
"ስብሐት ለማርያም እመ አምላክ እግዝእትነ ወመድኃኒትነ"
Photo unavailableShow in Telegram
🕊እንኳን አደረሳችኹ ወርኃ ታኅሣሥን በሰላም ያስፈጽመን የንስሐ ልብ ይሰጠን::
🕊"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::" /ማቴ ፫:፫/
💥ስለ ንስሐ💥
✝ከቅዱስ ሙሴ ጸሊም የምንማራቸው 7 ነገሮች።
፩, 🌿ቅዱስ አብርሃምን መምሰል( ፈጣሪውን ተመራምሮ አገኘ)::
፪, 🌿ዓለምንና የዓለምን ነገሮች መተው።
፫, 🌿የንስሐ ሕይወት( ንስሐን በትጋት መፈጸም)።
፬, 🌿መታዘዝ (የሚታዘዘውን ሳያጓድል መስራትን)።
፭, 🌿ለሌሎች መኖርን።
፮, 🌿በሰው አለመፍረድን።
፯, 🌿ትሕትናን።
1,💥ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡
2,💥ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡
3, 💥በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡
4,💥የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው
4 ነገሮችን በደንብ ልብ እንበል!
1, ✨አላማ
2 ,✨እምነት
3,✨ጥረት
4 ✨ጥንቃቄ
9ኙ የቅድስና መንገዶች
፩💥ሃይማኖት
፪💥ጾም
፫💥ጸሎት
፬💥ስግደት
፭💥ምጽዋት
፮💥ፍቅር
፯💥ትህትና
፰💥ትዕግስት
፱💥የዋህነት
✨እነዚኽን ያዟቸው ተጠቀሙባቸው
🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።
✝ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት
🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)
ለ ፳፻፲፯ የቤት ሥራ የሚሆኑ ፭ መልእክቶች
፩.ለጸሎት ተነሱ
፪.ክርስትናን መኖርን እንጀምር
፫.የእውነት ንስሐ ያስፈልገናል
፬.ካቆሸሸን ማኅበራዊ ሚዲያ ጥቂት እንራቅ
፭.ትልቁ መከራ እንዳያገኘን
🔗https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 12th of Tahisas
1. Abune Samuel of Waldiba
2. Sts. Anicetus and Photinus (Martyrs)
3. Abba Nedra (Hedra), Bishop of Aswan
4. St. John the Confessor (the Trusted)
5. Assembly of the Bishops (A Council in Rome against Novatus the Priest)
✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Michael the Archangel
2. St. Lalibela the Righteous (Emperor of Ethiopia)
3. St. John Chrysostom
4. St. Theodore the Eastern/El-Mishreke (the Oriental)
5. St. Kirstos Semra
6. St. Matthew the Apostle
7. St. Demetrius the Scholar
✞✞✞“ Bless them which persecute you . . . Rejoice with them that do rejoice, and weep with them that weep. Be of the same mind one toward another. Mind not high things, but condescend to men of low estate.”✞✞✞
Rom. 12:14-16
✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞
(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
https://t.me/zikirekdusn
✞And he labored for the service followed by wild beasts day and night. The Saint used to consume a moldy cabbage and water that had changed its color because of his strict austerity for the sustenance of his body.✞One day, our Savior, Christ, appeared and blessed him. And he anointed his body with His holy spittle. And at that moment, the Saint was filled with the Holy Spirit. And contemplating the passions of Christ, Abune Samuel used to prostrate thousands of times a day and lashed his back.
✞And he also fought by tying a chain to his legs. And with these deeds, he humiliated the demons and delighted his Creator. And after a while, Waldiba was filled with monks and disciples became numerous. And from the disciples Abba ZeRufael takes precedence.
✞Abune Samuel had a great love for our Lady. And he used to pray her Theotokia and Anaphora, and he used to praise her wholeheartedly. And while he did this, he used to rise a cubits length from the ground and hover.
✞And when his disciples were hungered, he used to turn water into white bread with the Anaphora of St. Mary.
As the scholar has said,
“While he blessed the water praying your anaphora
Samuel the bloom of faith changed it to bread, he of the desert of Waldiba
So that I speak the mercy and judgment of your miracle
Have my sins forgiven and lessen my trouble
Since Mary you can see to all”
(Mahlete Tsege)
✞And the Mother of Light for his love gave him a white gem, nourished him from a heavenly bread, and gifted him a heavenly incense. And the Saint censed with the Heavenly Priest for 12 years. And while the Virgin Mary had said to him, “I will intercede for him who like you recites the Theotokia and Anaphora (of St. Mary)” the Lord on the other hand blessed his monastery, Waldiba. The Lord had previously blessed the monastery during His flight to Egypt as well. As the accounts of the Saint are numerous, let us stop here for today. The Star of Waldiba, Abune Samuel passed away on this day, Tahisas 12 (December 21) in the year 1395 E.C. He was a 100 years old.
✞Honor is due for the Righteous.
✞✞✞Saints Anicetus and Photinus of Nicomedia✞✞✞
=>These Saints were brothers and the fruits of the Era of Persecution. When I think of their chronicle, it amazes me (the author). In their fiery age, their youth, preserved in faith, the love of Christ blazed upon them.
✞Loving Christ wholeheartedly and not just with the lips is truly what a fortune! The person who loves Christ will also have the love of His Virgin Mother and His beloved saints abundantly but not lessen in love.
✞The Saints Anicetus and Photinus, not being deceived by the life of the world, prepared themselves for martyrdom. And while different types of tortures that could even scare away wild beasts awaited them in line, they were not frightened.
✞First, the persecutors brought forth Anicetus. Then, they lashed him but he was not harmed. They burned him but he was not scorched. And then, they gave him to lions but they prostrated before him. Hence, Photinus, his brother, who was observing the scenes from the side, jumped into the arena of torments.
✞He then shouted out, “My brother is Christ’s; you won’t be triumphant over him.” And at that instant, many of the gentiles that were gathered there said, “The God of these youths is our God.” And the official in charge had the 2 Saints with many of [the converted] people beheaded.
✞And a sinner like I, shall pray in their name as follows.
“I say salutations to the followers of Anicetus
Who completed in fire their contest and race
Aid me to reach the chants of the angelic hosts
So that a destitute youth like me, poor of cognizance
Can beat the drums like the virgins”
(Arke)
✞✞✞May the God of Samuel keep our country from war and its people from flight by his intercession. And may He not deprive us from the Saints’ overflowing blessings.
Memhir Esuendale:
#Feasts of #Tahisas_12
✞✞✞On this day we commemorate the Departure of the Great Saint Abune Samuel of Waldiba and the Martyrs Anicetus and Photinus✞✞✞
✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞
✞✞✞ Abune Samuel of Waldiba ✞✞✞
=>Our country has bore myriads of saints. Not only in those past days that were blessed but today also we have many fathers and mothers that live in the deserts and caves who pray not only for the country but for the world.
✞And from the saints that rose in Ethiopia the “Samuels” have a unique place. In a time span of merely 20 years, the 6 Samuels came to be and showed the good path from a life of sanctity to evangelization, from the monastic life to asceticism. And these Saints were:
1. Samuel of Waldiba
2. Samuel of Tareta
3. Samuel of Qoyetsa
4. Samuel of Gish
5. Samuel of Hallelujah and
6. Samuel of Wegeg
✞Similarly, in Egypt, including the Star of Qalamun (the one who interceded for an angel named Qewestos before God) there have risen many Samuels. Our mothers, in the past, were proficient in giving names as Samuel means, “God has heard me”.
✞Coming back to what we have started, the Great Ethiopian Saint Abune Samuel was born in the 13th century (in 1295 E.C) in the city of Axum. His parents were called Estifanos (Stephen) and Amete Maryam.
✞Since the Saint’s lineage was from a priestly family, he studied the mysteries of the faith in his childhood. And it seems like that was the reason why he wanted to become an ascetic while he was just a teen.
✞Samuel, who obeyed and served his parents from his infancy, when he completed his education went to Debre Benkol. It is said that at the time, when he left for Debre Benkol, the Saint’s parents had departed. Debre Benkol is the monastery of Abune Medhanine Egzi the Great Star who was a father to the monks.
✞While Medhanine Egzi labored to become a luminary for the country; God gave him the 7 Stars. And from these, Abune Samuel takes precedence. And the rest included the fathers like Abune Yasay of Mandaba, Samuel of Tareta, Samuel of Qoyetsa and Yafekerene Egzi of Guguben.
✞Abune Samule with his 6 companions started his strife at Debre Benkol. He fetched water, grinded legumes, was obedient with his whole heart and side by side he studied patience, humility, austerity and the rites of a monastery from the Holy Abbot Abba Medhanine Egzi.
✞And because of his loved service, he pleased all. And at that moment, the Righteous Abbot brought forth Abune Samuel of Wali and the 6 Fathers to be tonsured as monks. And saying, “Axios - You deserve it!” he elevated them from being novices to monks.
✞And as light had descended and was seen when the 7 were being tonsured, they were called “Luminary Stars”. And they served there in the monastery for some time. However, because the relatives of Abune Samuel used to come and made things hard for the Righteous, all 7 Saints conversed and after being blessed by their father, Medhanine Egzi, left Debre Benkol.
✞Hence, all went to where the Holy Spirit guided them. The 3 (Samuel of Wali, Yasay of Mandaba and Yafekrene Egzi of Guguben) went to Lake Tana. And there, after staying together for some time, they separated for ministry. While Abune Yasay stayed at Mandaba and Abune Yafekrene Egzi at Guguben, islands in Lake Tana, Abba Samuel went to Waldiba.
✞Waldiba was established in the 5th century by the will of the Lord by 860 Saints. Nonetheless, because the founding Saints had become spirit-borne anchorites (sowah) the area was considered as a wilderness thus Abune Samuel re-established it.
✞The Saint, before he started his last austere strife, ministered the Gospel greatly. And after that, he made his dwelling with wild beasts. And as it can be seen in his icon, he rode a lion for years.
+እንደ እኔ ያለ ኃጢአተኛም በስማቸው እንዲህ ሊጸልይ ይገባል:-"ሰላም ዕብል ለአንቂጦስ ማሕበሮ::
እለ በእሳት ፈጸሙ ረዊጸ ወተባድሮ::
ያብጽሑኒእሉ ምስለ መላእክት ድርገተ ዘምሮ::
ህየ አኀሉ ወሬዛ ነዳየ ኩሉ አዕምሮ::
ኀበ ይዘብጣ ደናግል ከበሮ::" (አርኬ)
=>አምላከ ሳሙኤል በምጃቸው ሃገራችን ከጦርነት: ሕዝቦቿን ከስደት ይሰውርልን:: ሞልቶ ከተረፈ በረከታቸውም አይንሳን::
=>ታሕሳስ 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ
2.ቅዱሳን አንቂጦስ ወፎጢኖስ (ሰማዕታት)
3.አባ ነድራ
4.ቅዱስ ዮሐንስ ተአማኒ
5.ጉቡዓን ኤዺስ ቆዾሳት
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
3.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
4.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት)
5.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
6.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
7.ቅዱስ ድሜጥሮስ ሊቅ
=>+"+ የሚያሳድዷችሁን መርቁ . . . ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ:: ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ:: እርስ በርሳችሁ በአንድ አሳብ ተስማሙ:: የትዕቢትን ነገር አታስቡ:: ነገር ግን የትሕትናን ነገር ለመሥራት ትጉ:: +"+ (ሮሜ. 12:14-16)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
https://t.me/zikirekdusn
✝✞✝ ታኅሣሥ 12 ✝✞✝
✝✞✝ እንኩዋን ለታላቁ ጻድቅ "አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ" እና ለሰማዕታት "አንቂጦስ ወፎጢኖስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✝✞✝
+*" አባ ሳሙኤል ዘዋሊ "*+
=>ሃገራችን እልፍ አእላፍ ቅዱሳንን አፍርታለች:: እንኩዋን በተባረከው በቀደመው ዘመን ይቅርና ዛሬም ከሃገር ተርፈው ለዓለም የሚጸልዩ : በየበርሃውና በየፈርኩታው የወደቁ ብዙ አባቶችና እናቶች አሉን::
+በኢትዮዽያ ውስጥ ከተነሱ ቅዱሳን "ሳሙኤሎች" ልዩ ቦታ አላቸው:: በ20 ዓመታት ልዩነት ብቻ 6ቱ ሳሙኤሎች ተነስተው ከቅድስና ሕይወት እስከ ስብከተ ወንጌል : ከገዳማዊ ሕይወት እስከ ምናኔ በጐውን ጐዳና አሳይተዋል::
+እነዚህም:-
1.ሳሙኤል ዘዋልድባ
2.ሳሙኤል ዘጣሬጣ
3.ሳሙኤል ዘቆየጻ
4.ሳሙኤል ዘግሺ
5.ሳሙኤል ዘሃሌ ሉያ እና
6.ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ናቸው::
+በተመሳሳይም በግብጽ የደብረ ቀልሞኑን ኮከብ ጨምሮ (መልአኩን ቀውስጦስን ከጌታ ያማለዱት) ብዙ ሳሙኤሎች ተነስተዋል:: የድሮ እናቶቻችን በእውነት ስም መሰየሙን ይችሉበታል:: "ሳሙኤል" ማለት "ሰምዓኒ እግዚአብሔር ስዕለትየ - እግዚአብሔር ልመናየን ሰማኝ" ማለት ነውና::
+ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ታላቁ ኢትዮዽያዊ ጻድቅ አቡነ ሳሙኤል ዘዋሊ የተወለዱት በ13ኛው መቶ ክ/ዘመን (በ1295) በምድረ አክሱም ነው:: ወላጆቻቸውም እስጢፋኖስና ዓመተ ማርያም ይባላሉ::
+የዘር ሐረጋቸው ከካህናት ወገን ነውና ጻድቁ ገና በልጅነት ምሥጢራተ ሃይማኖትን ጠጥተዋል:: ለዚህም ይመስላል ገና ሕጻን ሳሉ ምናኔን የተመኙት::
+ከልጅነታቸው ጀምረው ወላጆቻቸውን ያገለገሉት ሳሙኤል ትምሕርታቸውን ሲፈጽሙ የተጉዋዙት ወደ ደብረ በንኮል ነበር::
በጊዜውም የጻድቁ ወላጆች ዐርፈው እንደ ነበር ይነገራል:: ደብረ በንኮል ማለት የታላቁ ኮከብና አበ መነኮሳት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ነው::
+መድኃኒነ እግዚእ ለሃገር ብርሃን የሆኑ ቅዱሳንን ያፈሩ ዘንድ ሲተጉ እግዚአብሔር 7ቱን ከዋክብት ሰጣቸው:: ክእነዚህ መካከልም ቀዳሚው አቡነ ሳሙኤል ናቸው:: ቀሪዎቹ ደግሞ እነ አቡነ ያሳይ ዘመንዳባ : ሳሙኤል ዘጣሬጣ : ሳሙኤል ዘቆየጻና ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤን የመሰሉ ናቸው::
+አቡነ ሳሙኤል ከ6ቱ ባልንጀሮቻቸው ጋር ሆነው በደብረ በንኮል ተጋድሎን አሐዱ አሉ:: እንጨት ይሰብራሉ:: ውሃ ይቀዳሉ:: እህል ይፈጫሉ:: በፍጹም ልባቸውም ይታዘዛሉ:: ጐን ለጐን ደግሞ ከቅዱሱ አበ ምኔት መድኃኒነ እግዚእ ጽንዓትን : ትሕትናን : ትሕርምትን ይማሩ : ሥርዓተ ገዳምንም ያጠኑ ነበር::
+ከአገልግሎታቸው ማማር የተነሳ ሁሉን ደስ ማሰኘት ቻሉ:: በዚህ ጊዜም ጻድቁ አበ ምኔት አቡነ ሳሙኤል ዘዋሊንና 6ቱን አበው ጠርተው ለምንኩስና አቀረቧቸው:: "ይገባቹሃል!" ሲሉም ከአሞክሮ ወደ ምንኩስና አሸጋገሯቸው::
+በዚያች ቀን 7ቱ ሲመነኩሱ ከሰማይ ብርሃን ወርዶ በመታየቱ ቅዱሳኑ "ከዋክብት ብሩሃን" ተባሉ:: ለተወሰነ ጊዜም በዚያው በገዳሙ አገለገሉ:: የአቡነ ሳሙኤል ዘመዶች ግን እየመጡ ጻድቁን ስላስቸገሩ 7ቱም ቅዱሳን ተመካክረው : ከአባታቸው መድኃኒነ እግዚእ ተባርከው ከደብረ በንኮል ወጡ::
+ሁሉም መንፈስ ቅዱስ ወደ መራቸው ሲሔዱ 3ቱ (ማለትም ሳሙኤል ዘዋሊ : ያሳይ ዘመንዳባና ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤ) ወደ ጣና ሔዱ:: በዚያም ለጥቂት ጊዜ አብረው ከቆዩ በሁዋላ ለአገልግሎት ተለያዩ:: አቡነ ያሳይ "መንዳባን" : አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ "ጉጉቤን" ይዘው እዛው ጣና አካባቢ ሲቀሩ አባ ሳሙኤል ወደ ዋልድባ ሔዱ::
+ዋልድባ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን በጌታ ፈቃድ የተመሠረተ ሲሆን 860ው መሥራች ቅዱሳን በመሠወራቸው እንደ ጠፍ ይቆጠር ነበርና አቡነ ሳሙኤል እንደ ገና አቀኑት::
+ጻድቁ በዋልድባ የመጨረሻውን ትሕርምት ከመያዛቸው በፊት በጊዜው ከፍተኛ የሆነ የወንጌል አገልግሎት ሰጥተዋል:: ቀጥለውም ኑሯቸውን ከግሩማን አራዊት ጋር አድርገዋል:: በስዕለ አድኅኖው እንደምናየው ለዘመናት በአንበሳ ጀርባ ላይ ተጭነዋል::
+ጧት ማታም ብዙ ግሩማን አራዊትን እያስከተሉ ለአገልግሎት ደክመዋል:: ጻድቁ ከትሕርምት ብዛት እህል ትተው የሻገተ ጐመንና መልኩን የለወጠ ውሃን ለቁመተ ሥጋ ይጠቀሙ ነበር::
+አንድ ቀንም መድኃኒታችን ክርስቶስ ወደ እርሳቸው መጥቶ ባረካቸው:: አካላቸውንም በቅዱስ ምራቁ አትቦ ቀባቸው:: በዚህ ጊዜም ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ተመሉ:: የክርስቶስን ሕማማት እያሰቡም እልፍ ጊዜ ይሰግዱ: ጀርባቸውን ይገርፉም ነበር::
+እግራቸውን በሰንሰለት አሥረው ይጋደሉም ነበር:: በዚህ ግብራቸው አጋንንትን አሳፍረው: ፈጣሪያቸውን ደስ አሰኙ:: ከቆይታ በሁዋላም ዋልድባ በመነኮሳት ተሞላ:: ደቀ መዛሙርት በዙ:: ቀዳሚው ግን አባ ዘሩፋኤል ጻድቅ ነው::
+አቡነ ሳሙኤል ከድንግል እመቤታችን ጋር ልዩ ፍቅር ነበራቸው:: ዘወትር ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በተመስጦ ያደርሱላት: ፈጽመውም ያመሰግኗት ነበር:: ይህንን ሲያደርጉ ከመሬት ክንድ ከፍ ብለው ይንሳፈፉ ነበር::
+ተከታዮቻቸው ሲርባቸውም ውሃውን በቅዳሴ ማርያም ነጭ ሕብስት ያደርጉት ነበር::
"ሶበ አተቦ ለማይ በቅዳሴኪ እንዘ ይጼሊ::
ረሰዮ ሕብስተ ሳሙኤል ጽጌ ሃይማኖት ዘሐቅለ ዋሊ::
ምሕረተ ወፍትሐ ለተአምርኪ እኅሊ::
ስረዪ ኃጢአትየ ወዕጸብየ አቅልሊ::
እስመ ኩሎ ገቢረ ማርያም ትክሊ::" እንዳለ ሊቁ:: (ማኅሌተ ጽጌ)
+እመ ብርሃንም ስለ ፍቅር ነጭ እንቁ ሰጠቻቸው:: ሰማያዊ ሕብስትን መገበቻቸው:: ንጹሕ ዕጣንንም አበረከተችላቸው:: ለ12 ዓመታትም ከሰማይ ካህናት ጋር አጠኑ:: ድንግል ማርያም "እንዳንተ ውዳሴየንና ቅዳሴየን በፍቅር የሚደግምልኝን አማልደዋለሁ" ስትላቸው:-
+ጌታ ደግሞ ገዳማቸውን ዋልድባን ቀድሷታል:: ቀድሞም በስደቱ ባርኩዋት ነበር:: የጻድቁ ዜና ፈጽሞ ብዙ ነውና ለዛሬ በዚህ ይብቃን:: የዋልድባው ኮከብ አቡነ ሳሙኤል ያረፉት ታሕሳስ 12 ቀን በ1395 ሲሆን ዕድሜአቸውም 100 ዓመት ነበር::
<< ለጻድቁ ክብር ይገባል !! >>
+"+ ቅዱሳን አንቂጦስ ወፎጢኖስ +"+
=>እነዚህ ቅዱሳን በሥጋ ወንድማማቾች ሲሆኑ የዘመነ ሰማዕታት ፍሬዎች ናቸው:: ዜና ሕይወታቸውን ሳስበው ይገርመኛል:: በእሳት የወጣትነት ዘመናቸው በሃይማኖት ጸንተው: ፍቅረ ክርስቶስ እንደ እሳት በላያቸው ላይ ይነድ ነበር::
+በእውነት ክርስቶስን በከንፈር ያይደለ በፍጹም ልቡና መውደድ እንዴት ያለ መታደል ነው! ክርስቶስን የወደደ የድንግል እናቱና የቅዱሳን ወዳጆቹ ፍቅር ይበዛለታል እንጂ አይቀንስበትም::
+ቅዱሳኑ አንቂጦስና ፎጢኖስ ወጣትነት: የዓለም ኑሮ ሳያታልላቸው ለሰማዕትነት ራሳቸውን አዘጋጁ:: እንኩዋን ሰውን አራዊትን የሚያስበረግግ የስቃይ ዓይነት ተሰልፎ ሳለ በፍጹም አልደነገጡም::
+መጀመሪያ አንቂጦስን አቀረቡት:: ገረፉት: ምንም አልሆነም:: በእሳት አቃጠሉት: ምንም አልነካውም:: ለአንበሳ ሰጡት: እነርሱ ግን ሰገዱለት:: ከዳር ሆኖ ይህንን ሁሉ ሲመለከት የነበረው ወንድሙ ፎጢኖስ ዘሎ ወደ መከራ አደባባይ ገባ::
+"ወንድሜ የክርስቶስ ነውና መቼም አታሸንፈውም" ሲል ጮኸ:: በዚህ ጊዜም በሥፍራው የነበሩ ብዙ አሕዛብ "የእነዚህ ወጣቶች አምላክ አምላካችን ነው" አሉ::
መኮንኑም 2ቱን ቅዱሳን ከብዙ ሕዝብ ጋር አሰይፏቸዋል::
Photo unavailableShow in Telegram
✝እንኳን አደረሳችሁ !
☞ወርኀ ታኅሣሥ ቡሩክ።
ወአመ ፲ወ፩፦
✝ጾመ ስብከተ ጌና፥ ዘነቢያት ወዘአበው ቀደምት ቅዱሳን (ወይእቲ ጾመ አዳም)
✝ተዝካረ ጥምቀቱ ለመድኅን ክርስቶስ (ዘሎቱ ስብሐት ወአኮቴት)
✝ወተዝካረ በዓሎሙ ለቅዱሳን፦ ኢያቄም ወሐና፥ ፋሲለደስ ወሐራ ድንግል፥ ወያሬድ ካህን
❖ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ጻድቅ ወንጹሕ፥ አባ በኪሞስ ገዳማዊ፥ መነኮስ ሐዋርያዊ፥ ዘሀገረ መጺል (ወቢጹ ለአባ ሲኖዳ አርሲመትሪዳ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ማር ገላውዴዎስ ድንግል ወሰማዕት፥ አርአያ መላእክት፥ እመዘመደ መንግሥት፥ ወመዋዒ በውስተ ጸብዕ (ልደቱ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ አባ በርተሎሜዎስ ኤጲስ ቆጶስ
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ቴዎድሮስ ሰማዕት፥ ፍሱሐ ገጽ
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ በጥላን ሰማዕት
❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡
https://t.me/zikirekdusn
Photo unavailableShow in Telegram
ታኅሳስ ፲፩
"" ✝ማር ገላውዴዎስ✝ ""
"ተወዳጅ ሰማዕት"
"" የልደቱ በረከት ይደርብን:: ""
https://t.me/zikirekdusn
Photo unavailableShow in Telegram
🕊እንኳን አደረሳችኹ ወርኃ ታኅሣሥን በሰላም ያስፈጽመን የንስሐ ልብ ይሰጠን::
🕊"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::" /ማቴ ፫:፫/
ለ ፳፻፲፰የቤት ሥራ የሚሆኑ ፯መልእክቶች
፩,እንጸልይ::
፪,አፋችንን እጃችንን እግራችንን እንሰብስበው::
፫, ከቆሻሻ ኢንተርኔት ራሳችሁን አርቁ። የምትከታተሉትን ምረጡ!
፬,ምጽዋት እንስጥ።
፭,ንሰሐ እንግባ።
፮,እንዘን እናልቅስ።
፯, ለሁሉም ነገር እንዘጋጅ
💥ስለ ንስሐ💥
✝ከቅዱስ ሙሴ ጸሊም የምንማራቸው 7 ነገሮች።
፩, 🌿ቅዱስ አብርሃምን መምሰል( ፈጣሪውን ተመራምሮ አገኘ)::
፪, 🌿ዓለምንና የዓለምን ነገሮች መታው።
፫, 🌿የንስሐ ሕይወት( ንስሐን በትጋት መፈጸም)።
፬, 🌿መታዘዝ (የሚታዘዘውን ሳያጓድል መስራትን)።
፭, 🌿ለሌሎች መኖርን።
፮, 🌿በሰው አለመፍረድን።
፯, 🌿ትሕትናን።
1,💥ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡
2,💥ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡
3, 💥በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡
4,💥የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው
4 ነገሮችን በደንብ ልብ እንበል!
1, ✨አላማ
2 ,✨እምነት
3,✨ጥረት
4 ✨ጥንቃቄ
9ኙ የቅድስና መንገዶች
፩💥ሃይማኖት
፪💥ጾም
፫💥ጸሎት
፬💥ስግደት
፭💥ምጽዋት
፮💥ፍቅር
፯💥ትህትና
፰💥ትዕግስት
፱💥የዋህነት
✨እነዚኽን ያዟቸው ተጠቀሙባቸው
እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።
✝ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት
ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን!
(የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🔗https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
✞✞✞May the God of Abba Pijimi (Bakimos) not deprive us from His grace and honor. And may He grant us from his blessings.✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 11th of Tahisas
1. The Great Abba Pijimi (Bakimos)
2. St. Bartholomew
3. St. Theodore
4. St. Betlan (Panteleon)
✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Yared (Jared) Priest and Chanter
2. Mar Claudius the Martyr
3. St. Basilides the Martyr
4. Abune Hara Dengel the Righteous
5. The Blessed Anna
✞✞✞“Know ye not that they which run in a race run all, but one receiveth the prize? So run, that ye may obtain. And every man that striveth for the mastery is temperate in all things. Now they do it to obtain a corruptible crown; but we an incorruptible.”✞✞✞
1 Cor. 9:24-25
✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞
(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
And when he became 39 years old, he even went further inwards into the desert which was more isolated.
✞And the place he reached was where the sun scorched like fire and the earth was as searing as a pan. Nevertheless, the Good God grew for this great man one palm tree and brought forth a small spring.
✞Abba Pijimi (Bakimos) then started his main strife here. He frequented fasting, prayer and prostration. He first fasted for 3 days, then for 7 days and finally he ate only once in 40 days.
✞And his meal was a handful of dates and a cheek full of water. Beyond this, he did not want to give his body an excuse or luxury. And for this reason, his body withered and his physique changed. However, he was strong and joyful, and a tireless fighter.
✞And what was amazing was his prayer. Without counting his other devotions, he used to recite “Our Father” 2,400 times during the day with a unique contemplation. And in the evening, he recited it the same number of times. And in total he used to pray “Our Father” 4,800 times a day.
✞And who could count his prostrations! The Great Abba Pijimi (Bakimos) stayed for 24 years in such a strife and his age reached 63 years. At one time, he stayed for 80 days meditating on the passions of Christ. And when he became famished, a holy angel brought down for him a heavenly bread and a heavenly drink.
✞The angel then ascended to heaven after nourishing him from the bread and letting him drink from the chalice. And when he ascended, he left him the bread. And he instructed him, “Always eat from this.” And Abba Pijimi (Bakimos) starting from that day ate from the bread until the day of his departure. And the meal did not exhaust.
✞And in the days of Abba Pijimi (Bakimos) fathers like Abune Kiros/Karas/Cyrus and the Great Shenouda lived s well. Particularly, Abba Shenouda the Archimandrite and Abba Pijimi (Bakimos) were introduced to one another as follows by the Holy Spirit.
✞One day, Abba Shenouda saw a pillar of gems stretched from the earth to heaven and he asked, “Lord! What is the mystery behind it?” and he heard a voice that said, “This pillar is Abba Pijimi (Bakimos). Go and meet him.” Hence, Abba Shenouda travelled by foot and met Abba Pijimi (Bakimos).
✞And after they exchanged greetings, Abba Pijimi (Bakimos) said to Shenouda the Great, “Let me prepare the meal and you fetch the water”. And when St. Shenouda stepped outside, filled the vessel miraculously and returned, Abba Pijimi (Bakimos) awaited him with the meal ready but without fire being started.
✞Both amazed, exchanged smiles and knew of one another’s sanctity. After they went for a bit in the desert, they became tired and sat down. And before them they saw a human skull and tapping it with their staffs, they said, “Hey you! Rise and speak with us.”
✞And that skeleton rose as a full man and prostrated before them. They then asked, “From where have you come?” and the person replied, “From hell.” Then, he told them that he was a heathen and was in hell in much torment. And he added, “And there are many below us that say they are Christians but who trifled their Christianity. And their tortures can’t even be told.”
✞After which, they again tapped him with their staff and returned him to his prior state. After that, they bid farewell to one another and left to each of their own cells. Then, the Great Abba Pijimi (Bakimos) for the next 7 years preached the Gospel being taken up by the wings of an angel. And he brought many to the faith and repentance.
✞And he always used to weave and sell baskets. And he was compassionate with the earnings towards the destitute. And an angel used to take him to wherever he wanted. The Great Abba Pijimi (Bakimos) departed on this day 58 years after he entered the desert at the age of 70 years. And he has inherited the glory of glories.
Memhir Esuendale:
#Feasts of #Tahisas_11
✞✞✞On this day we commemorate the Departure of Abba Pijimi (Bakimos)✞✞✞
✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞
✞✞✞Abba Pijimi (Bakimos) the Great✞✞✞
=>According to the Church’s teaching, fathers that are named “the Great” are exceptional. And it is given because they have accomplished many virtues. And we distinguish with it saints that have similar names.
✞The background for the ascetic life is the Old Testament. It is believed that the children of Seth who lived on the Holy Mount (Debre Kidus) began it. However, the life was shown vividly by the Great Enoch - the Righteous and then by the Holy Priest Melchizedek.
✞Thereafter, St. Elijah, the Prophet and his disciple Elisha lived it. And in the New Testament St. John the Baptist, who spent his whole life in the desert, takes precedence.
✞Our Savior Christ, to Whose name’s invoking be prostration, has sanctified and taught the ascetic life by living in the Judean Desert for 40 days. And His cell that He used during His ministry for spending the night found in Mt. Olive (Elion cave) by itself is a great example of such a life.
✞Historical texts show that after the ascension of the Lord, when the Apostles become weary of the clatter of the world or when they wanted to serve their Creator with a pure and composed heart, they used to go outside the cities. And there, they lived in groups or alone. The main thing here is that they were diligent in fasting and prayer. And this passed down and reached to the 3rd century. At that time, a pure Christian named Abba Paul took this life to an advanced level. He struggled for 80 years without being seen by anyone and was called “The Father of the Hermits”. And he started asceticism that had order.
✞And 20 years after that transpired, a kind Christian named Abba Anthony sweetened the ascetic life in another way. The ascetic life was tuned when St. Michael gave the monk's habit [to St. Anthony]. Thus, Abba Anthony was named as “The Father of the Monks”.
✞And to expand the life he received disciples from different countries and tonsured them monks. And the Saints, the spiritual children of Abba Anthony, returned to their respective countries, showed the life practically and expanded monasticism.
✞Abba Pijimi (Bakimos) [one of the spiritual descendants of Abba Anthony] was a father whose name’s invocation was honored, he was a revered elder, a hermit of good old age, a monk and an apostolic. He live in the Era of the Righteous (in the 5th century) and was from Upper Egypt (Southern Egypt) like many of the then saints.
✞Abba Pijimi (Bakimos) after he was born from Christian parents studied Christianity in his childhood and became a shepherd. And as he kept sheep, the call of God reached him. At that time, he was just 12 years old.
✞And he was called as follows. While he was shepherding, the Angel of the Lord appeared to him in the form of a man. Then, the Seraph sat and spoke to him for some time about the honor of asceticism. Afterwards he asked him, “Why don’t you and I become ascetics so that we could have this honor?”
✞Hence, the adolescent Pijimi (Bakimos) joyously said, “Okay”. And immediately, he returned the sheep to his parents and went to a monastery with the angel. And while they were traveling, the holy angel told him about many mysteries, strengthened him and indwelt in him the grace of God.
✞However, when they reached a monastery (Scete), the angel disappeared from him. Then, St. Pijimi (Bakimos) entered into the monastery and started the ascetic life. As he was young, serving the elders, he studied well the rites of monasticism, austerity, silence and strife.
✞There, he was tonsured a monk as well. And after he served for 24 years and when he was 36 years old, he wished for the life of the hermits. And after he received the blessing of the fathers, he went to the empty desert chanting.✞And at one place, he prayed for 3 years without being discouraged by the heat of the day and the cold of the night.
አምጥቷል::
+ሁሌም እንቅቦችን እየሰፋ ይሸጥ: በዋጋውም ለነዳያን ይራራ ነበር:: መልአኩም ወደ ፈለገበት ቦታ ተሸክሞ ይወስደው ነበር:: ታላቁ ቅዱስ አባ በኪሞስ በርሃ በገባ በ58 ዓመቱ : በተወለደ በ70 ዓመቱ በዚህች ቀን ዐርፏል:: የክብር ክብርንም ወርሷል::
=>አምላከ አባ በኪሞስ ጸጋውን: ክብሩን አይንሳን:: ከበረከቱም ይክፈለን::
=>ታሕሳስ 11 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ታላቁ አባ በኪሞስ
2.ቅዱስ በርተሎሜዎስ
3.ቅዱስ ቴዎድሮስ
4.ቅዱስ በጥላን
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ያሬድ ካህን
2.ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት
3.ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
4.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ
5.ቅድስት ሐና ቡርክት
=>+"+ በእሸቅድምድም ሥፍራ የሚሮጡት ሁሉ እንዲሮጡ: ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ:: የሚታገልም ሁሉ በነገር ሁሉ ሰውነቱን ይገዛል:: እነዚያም የሚጠፋውን አክሊል ሊያገኙ ነው:: እኛ ግን የማይጠፋውን:: +"+ (1ቆሮ. 9:24)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ፡፡ አሜን፡፡ ✞✞✞
=>+"+ እንኩዋን ለታላቁ "ጻድቅና ገዳማዊ አባ በኪሞስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"+
+*" ታላቁ አባ በኪሞስ "*+
=>በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ "ታላቁ : ዓቢይ : (THE GREAT)" የሚል ስም የሚሰጣቸው አባቶች የተለዩ ናቸው:: አንድም እጅግ ብዙ ትሩፋቶችን የሠሩ ናቸው:: በሌላ በኩል ደግሞ በተመሳሳይ ስም ከሚጠሩ ሌሎች ቅዱሳን እንለይበታለን::
+ገዳማዊ ሕይወት ጥንቱ ብሉይ ኪዳን ነው:: በቀዳሚነትም በደብር ቅዱስ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ደቂቀ ሴት እንደ ጀመሩት ይታመናል:: ሕይወቱ በጐላ: በተረዳ መንገድ የታየው ግን በታላቁ ጻድቅ ሄኖክ: ከዚያም በቅዱሱ ካህን መልከ ጼዴቅ አማካኝነት ነው::
+ቀጥሎም እነ ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ : እነ ኤልሳዕ ደቀ መዝሙሩ ኑረውበታል:: በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ሙሉ ሕይወቱን በገዳም (በበርሃ) ያሳለፈው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቅድሚያውን ይይዛል::
+ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና መድኃኒታችን ክርስቶስ በገዳመ ቆረንቶስ ለ40 ቀናት በትሕርምት ኑሮ ገዳማዊ ሕይወትን ቀድሷል:: አስተምሯል:: በዘመነ ስብከቱም ያድርባት የነበረችው የደብረ ዘይቷ በዓቱ (ኤሌዎን ዋሻ) በራሷ ለዚህ ሕይወት ትልቅ ማሳያ ናት::
+ከጌታ ዕርገት በሁዋላም ክርስቲያኖቹ የዓለም ሁካታ ሲሰለቻቸው: አንድም በንጹሕና በተሸከፈ ልቡና ለፈጣሪያቸው መገዛትን ሲሹ ከከተማ ወጣ እያሉ ይኖሩ እንደ ነበር የታሪክ መዛግብት ያሳያሉ:: አኗኗራቸውም በቡድንም: በነጠላም ሊሆን ይችላል::
+ዋናው ነገር ግን በጾምና በጸሎት መትጋታቸው ነው:: ይሕም ሲያያዝ እስከ 3ኛው መቶ ክ/ዘመን ደረሰ:: በዚህ ዘመን ግን አባ ዻውሊ የሚባል አንድ ንጹሕ ክርስቲያን ይሕንን ሕይወት ወደ ሌላ ደረጃ ከፍ አደረገው:: ለ80 (90) ዓመታት ሰው ሳያይ ተጋድሎ "የባሕታውያን አባት" ተባለ:: ደንብ ያለው ተባሕትዎም ጀመረ::
+ይህ ከሆነ ከ20 ዓመታት በሁዋላ ደግሞ አባ እንጦንስ የሚባሉ ደግ ክርስቲያን ይህንን ገዳማዊ ሕይወት በሌላ መንገድ አጣፈጡት:: በቅዱስ ሚካኤል አመንኩዋሽነት ገዳማዊ ሕይወት በምንኩስና ተቃኘ:: ስለዚህም አባ እንጦንስ "የመነኮሳት አባት" ተባሉ::
+እርሳቸውም ሕይወቱን ለማስፋፋት ከተለያዩ አሕጉር ደቀ መዛሙርትን እየተቀበሉ አመንኩሰዋል:: ቅዱሳን የአባ እንጦንስ ልጆችም ወደየ ሃገራቸው ተመልሰው: ሕይወቱን በተግባር አሳይተው ገዳማዊነትን አስፋፍተዋል::
=>አባ በኪሞስ ስም አጠራሩ እጅግ የከበረ: ሽምግልናው ያማረ ባሕታዊ: መነኮስና ሐዋርያዊ አባት ነው:: የነበረው በዘመነ ጻድቃን (በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን) ሲሆን ትውልዱ እንደ ብዙዎቹ የወቅቱ ቅዱሳን በላይኛው (በደቡብ) ግብጽ ነው::
+አባ በኪሞስ ከክርስቲያን ወላጆቹ ተወልዶ: በልጅነቱ ክርስትናን አጥንቶ በእረኝነት ተሰማራ:: በጐቹን ሲጠብቅም የእግዚአብሔር ጥሪ ወደ እርሱ መጣ:: ያኔም እድሜው ገና 12 ዓመት ነበር::
+አጠራሩም እንዲህ ነው:: በእረኝነት ሳለ መልአከ እግዚአብሔር ሰው መስሎ መጥቶ ተገናኘው:: ቁጭ ብሎም ስለ መናንያን ክብር ሲያጫውተው ከዋለ በሁዋላ "ለምን እኔና አንተ ለዚህ ክብር እንድንበቃ አንመንንም?" ሲል ጠየቀው::
+ሕጻኑ በኪሞስም ደስ ብሎት "እሺ!" አለው:: ወዲያውም መንጋውን ለወላጆቹ መልሶ ከመልአኩ ጋር ወደ ገዳም ሔዱ:: ቅዱሱ መልአክም በመንገድ ሳሉ ብዙ ምሥጢራትን ነገረው:: አጸናው:: ረድኤተ እግዚአብሔርንም አሳደረበት::
+ልክ ወደ አንድ ገዳም ሲደርሱ ግን ተሰወረበት:: ቅዱስ በኪሞስም ወደ ገዳሙ ገብቶ ይምናኔ ሕይወትን ጀመረ:: በዚያም እንደ ልጅነቱ አበውን እያገለገለ: ሥርዓተ ገዳምን: ትሕርምትን: አርምሞንና ተጋድሎን በደንብ አጠና::
+በዚያው ገዳም ሳለም ምንኩስናን ተቀበለ:: ለ24 ዓመታት አገልግሎ 36 ዓመት በሞላው ጊዜም ተባሕትዎን ተመኘ:: ከአባቶች ዘንድ ተባርኮም ጭው ወዳለው በርሐ እየዘመረ ተጉዋዘ::
+አንዲት ቦታ ላይም የቀኑን ሐሩር: የሌሊቱን ቁር ሳይሰቀቅ ለ3 ዓመታት ጸለየ:: እድሜው 39 ዓመት ሲሆን እንደ ገና ጭራሽ ፍጥረት ወደ ማይደርስበት በርሃ ተጉዞ ደረሰ::
+የደረሰበት አካባቢ ፀሐይ እንደ እሳት የምታቃጥልበት: ምድር እንደ ብረት ምጣድ የጋለችበት ነው:: ቸር እግዚአብሔር ግን ለዚህ ታላቅ ሰው አንዲት የተምር ዛፍ አበቀለለት:: ትንሽ ምንጭንም አፈለቀለት::
+አባ በኪሞስም ዋናውን ተጋድሎ በዚህ ሥፍራ ጀመረ:: ጾምን : ጸሎትን : ስግደትን ያዘወትር ነበር:: ጾሙ በመጀመሪያ 3 ቀን: ቀጥሎ 7 ቀን: በመጨረሻ ግን በ40 ቀን አንዴ ብቻ ማዕድ የሚቀምስ ሆነ::
+ለዛውም ምግቡ አንዲት እፍኝ ይቆረጥማል:: አንዲት ጉንጭ ውሃን ይጐነጫል:: ከዚህ በላይ ለሥጋው ምክንያትና ምቾትን ሊሰጣት አልፈለገም:: በዚህም ምክንያት አካሉ ደርቆ ከሰውነት ተራ ወጣ:: ግን ብርቱና ደስተኛ: የማይደክምም ተዋጊ ነበር::
+የሚገርመው ደግሞ ጸሎቱ ነው:: ሌሎች ጸሎቶቹ ሳይቆጠሩ በመዓልት (በቀን) 2,400 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን በልዩ ተመስጦ ያደርሰው ነበር:: በሌሊትም በተመሳሳይ ቁጥር ይደግመዋል:: በድምሩ በየዕለቱ 4,800 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት ይል ነበር::
+ስግደቱንማ ማን ቆጥሮት! ታላቁ አባ በኪሞስ እንዲህ ባለ ገድል ለ24 ዓመታት ቆየ:: እድሜውም 63 ደረሰ:: አንድ ጊዜ ግን ሕማማተ ክርስቶስን እያሰበ ያለ ምግብ ለ80 ቀናት ቆየ:: ፈጽሞ በተራበ ጊዜም ቅዱስ መልአክ ከሰማይ ሕብስተ በረከቱን: ጽዋዐ አኮቴቱን ይዞለት ወረደ::
+ከሕብስቱ መግቦት: ከጽዋው አጠጥቶት ወደ ሰማይ ዐረገ:: ሲያርግ ግን ሕብስቱን ትቶለት ነበር:: "ዘወትርም ከዚህ ተመገብ" ብሎታል:: አባ በኪሞስም ከዚያች ቀን ጀምሮ እስከ ዕረፍቱ ድረስ የተመገበው ከዚያ ሕብስት ነው:: ግን አላለቀም ነበር::
+በታላቁ አባ በኪሞስ ዘመን እነ አቡነ ኪሮስና ታላቁ ሲኖዳን የመሰሉ አበው ነበሩ:: በተለይ የባሕታውያን ሁሉ አለቃ አባ ሲኖዳና አባ በኪሞስን መንፈስ ቅዱስ እንዲህ አስተዋውቁዋቸዋል::
+አንድ ቀን አባ ሲኖዳ የእንቁ ምሰሶ ከምድር እስከ ሰማይ ተዘርግቶ ያይና "ጌታየ! ምሥጢሩ ምንድን ነው?" ቢል "ይህ ምሰሶ አባ በኪሞስ ነውና ሒድ ተገናኘው" የሚል ቃልን ሰማ:: አባ ሲኖዳም በእግሩ ተጉዞ አባ በኪሞስን አገኘው::
+ሰላምታን ከተለዋወጡ በሁዋላ አባ በኪሞስ ታላቁ ሲኖዳን "እኔ ወጥ ልሥራ: አንተ ውሃ ቅዳ" አለው:: ቅዱስ ሲኖዳ ከበር ብቅ ብሎ ማሰሮውን በተአምራት ውሃ ሞልቶት ሲመለስ አባ በኪሞስ ደግሞ ያለ እሳት ወጡን አብስሎት ቆየው::
+2ቱም ተገርመው ፈገግታን ተለዋወጡ:: ማንነታቸውንም ተዋወቁ:: ለመናፈስ ወደ በርሃ ወጥተው ሳለም ደክሟቸው ቁጭ አሉ:: ከፊታቸው አንድ የሰው ራስ ቅል ነበርና በበትራቸው መታ : መታ አድርገው "አንተ! ተነስ አጫውተን" አሉት::
+ያ አጽምም ሥጋ ነስቶ: ተነስቶ ሰገደላቸው:: "ከወዴት መጣህ?" ቢሉት "ከሲዖል" አላቸው:: አረማዊ እንደ ነበርና የሲዖልን የመከራ ብዛት ነገራቸው:: አክሎም "ክርስቲያን ነን እያሉ በክርስትናቸው የሚቀልዱ ከእኛ በታች በብዛት አሉ:: መከራቸው ተነግሮ አያልቅም" አላቸው::+ድጋሚ በበትራቸው ነክተው ወደ ነበረበት መለሱ:: ከዚያም ቅዱሳኑ ወደየ በዓታቸው ተሰነባበቱ:: ታላቁ አባ በኪሞስ ከዚህ በሁዋላ ለ7 ዓመታት ያህል መልአክ በክንፉ እየወሰደው ወንጌልን ሰብኩዋል:: ብዙዎችንም ወደ ሃይማኖትና ንስሃ
