es
Feedback
ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)

Ir al canal en Telegram

በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

Mostrar más
2025 año en númerossnowflakes fon
card fon
50 485
Suscriptores
-624 horas
+27 días
+10030 días
Archivo de publicaciones
✞But my dear brothers and sisters let us be careful as people who are of the flesh that are trading in the name of our holy mother have increased. As the glory of the martyr is ample, let us not only relay on dreams. As St. Anthony said, “He who believes in dreams is a fool.” ✞On this day we should also commemorate with the martyr, St. Agatha. This mother was an Abbess and she taught, consoled and stood by St. Arsema. She has also shared from all the trials, hunger, thirst and flight of the martyr. And in the end, was beheaded together with her. ✞This day is the day on which the relics of St. Arsema and her follower martyrs were translocated and the consecration of her church took place. ✞✞✞Abba Abraham and Saint Simeon the Cobbler✞✞✞ =>This 2 stars were fathers that rose in the 11th century in the Land of Egypt and performed an astounding miracle for the Church. And they did not know of one another until the Virgin Mary brought them together for a task. ✞✞✞Abba Abraham✞✞✞ =>This Saint’s lineage was from Syria and was a renowned merchant. And he was wealthy from his trade by going back and forth from Syria to Egypt. Nevertheless, because he was a man that was well versed in Christianity, did not disregard the poor, did not avoid fasting and prayer and was not a person that wanted luxury for himself only, God called him for a greater vocation. ✞When the 61st Patriarch of Egypt, Abba Mina ll (some say Philotheos) departed and the fathers wanting to find his successor held fasts and prayers, God told them, “Appoint Abraham the Syrian”. Though he said, “No”, they did not let him go. After he said if it is the will of God and distributed half his wealth to the poor and the rest to monasteries, he sat on his See. And during his office, he has labored much to remove the habit of sin [from the faithful]. ✞✞✞Saint Simeon the Cobbler✞✞✞ =>He was a father that lived in the same era around Misr (in present-day Cairo) in complete humility in prayer and fasting by hiding himself, mending shoes, feeding the destitute and aiding the weak.  He has also gouged out his eye with a hand stitcher when one youthful woman went to entice him. ✞✞✞When Faith Moves a Mountain✞✞✞ =>The Caliph of the time, El-Mu'izz, because he loved philosophy, used to hold debates for scholars. And one Jew, who thought himself to be a scholar, asked for permission wanting to debate Christians. Hence, Abba Abraham and Abba Severus went, were victorious, humiliated him and left. ✞And the Jew holding a grudge took the verse on Matt. 17:20 and presented it to the Caliph. The verse said, “If ye have faith as a grain of mustard seed, ye shall say unto this mountain, Remove . . . it shall remove”. ✞Then, the Caliph summoned Abba Abraham and asked, “Does your Holy Bible say this?” To which Abba Abraham answered by saying, “Yes!” And when the Caliph reiterated, “Do it and show me”, the father asked for 3 days and left. Thence, while all of the faithful held a vigil of prayer for 3 days, Abba Abraham wept for 3 days without consuming food or sleeping in the Church of the our Lady. ✞Then, the Mother of Light appeared to him in glory and said, “Simeon the Cobbler will perform this for you.” He then led by a mark went to him and bowing before him said, “Have compassion for your kinsfolk the Christians?!”    ✞And so that the Saint in shock will not say no, the father invoked the name of the Virgin Mary. Thus, Saint Simeon said to Abba Abraham, “I don’t want to be recognized by men!” and they went to one great mountain (Mukatam). ✞There, the people stood on one side while the Caliph and his soldiers stood on the other face of the mountain. When the Saints together with the faithful prayed, “Kyrie Eleison -Lord, have mercy” 41 times, prostrated and rose, the mountain was removed from the ground and floated in the air. And to strengthen the proof, it was removed and put back 3 times.
Mostrar todo...
የዲ/ዮርዳኖስ አበበ ትምህርቶች የሚተላለፉበት ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት: #Feasts of #Tahisas_6 ✞✞✞On this day we commemorate the Virgin and Martyr Saint Arsema (Hripsime), Abba Abraham and Saint Simeon the Cobbler✞✞✞ ✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞ ✞✞✞ Saint Arsema (Arbsima/Repsima/Hripsime) the Virgin ✞✞✞ =>With what could we symbolize our mother St. Arsema? As she is a gem that sits on the horizon and shines, her honor is immeasurable. As Christ our Savior has said in the Gospel, “A city that is set on a hill cannot be hid” (Matt. 5:14), the life of this martyr is seen revealed like light before us. *St. Arsema is blessed since she grew up as a child obeying her parents. *St. Arsema was a flawless beauty. *St. Arsema was a virgin. *St. Arsema was a righteous ascetic. *And St. Arsema is a powerful martyr. If asked, “How that came to be?”, it was as follows. ✞According to what the fathers have told us in Tradition, St Gregory [the Illuminator] was the elder brother of the great martyr St. Arsema (Hripsime). And according to what is written in the Chronicles of the Martyrs, in that Era of Persecution, St. Gregory had three duties. 1. Consoling the martyrs including St. Arsema. 2. Learning well (to be versed in) the teachings of the Church. 3. And preparing himself for the trials that were about to come. ✞Because the Saint accomplished all three well; he became the model for the rest. He also made that pure warrior St. Arsema to steadfast and be a leader to the virgins. And they prayed, fasted and did ascetic activities living in a monastery until tribulation reached them. ✞This is why we call St. Arsema and St. Gregory righteous. However, later, because Diocletian, the abode of Satan, attracted by the beauty of St. Arsema said that he wanted to marry her, St. Gregory fled to Armenia taking 127 Christians including the Virgin Arsema.  ✞In Armenia, they stayed hidden for some time in one monastery in prayer and fasting until hunger overcame them. And because there was nothing to eat in the area St. Gregory was forced to leave to the city.  ✞There, he was hired as a slave in the palace of Tiridates (the III). And with the money he made, he used to help his kinfolk. Nevertheless, the trials did not leave them. The accursed Diocletian heard that the Saints had gone to Armenia and he sent Tiridates to capture and send them to him. ✞But when Tiridates saw St. Arsema, he could not contain himself because of her beauty and asked her saying; “I want to marry you”. However, the Virgin told him, “I am the bride of Christ. It won’t happen.” Then, he tried to intimidate her. And while she saw, he slaughtered the virgins. ✞And when he was unsuccessful, he tried to force her to marry him in public but she twisted his hand and dropped him to the ground in front of everyone. And because he was highly embarrassed, he had her whipped, tortured and had her eyes to be taken out.  Finally, he had her beheaded and thrown with [the bodies of] the martyrs on a mountain. ✞After all these, when Tiridates and his servants went hunting, evil spirits altered them to the forms of beasts (wild boars). ✞The King’s shift into an animal created a great fright in Armenia. And when the King’s sister cried, in a vision, she heard, “You won’t be saved unless you bring forth Gregory from where he is buried”. Straightaway, they dug him out. ✞When the Saint was taken out, he did not seek rest. He collected the relics of St. Arsema and the Martyrs, which have had no one to bury, and he placed their relics with honor after 15 years [of their martyrdom]. Then, he went to the desert and healed Tiridates and his servants. ✞Our fathers have told us in Tradition that the relics of the martyr St. Arsema with other martyrs’ relics were brought to our country (Ethiopia) in the 14th century. And this seems to be why our blessed mother loves Ethiopians for the most part than others (other nations). Including in her main monastery (found in Wollo/Kulamaso/Se’ba), she does great wonders where her name is invoked.
Mostrar todo...
+እመ ብርሃን በሞገስ መጥታ "ጫማ ሰፊው ስምዖን ይህንን ያደርግልሃል" አለችው:: በምልክት ሒዶ: በፊቱ አዘንብሎ "አቤቱ ለገኖችህ ክርስቲያኖች ራራላቸው?" አለው::+ቅዱሱ ደንግጦ እንቢ እንዳይለው የድንግል ማርያምን ስም ጠራበት:: ቅዱስ ስምዖንም ለአባ አብርሃም "ሰው እንዳያውቀኝ አደራ!" ብሎት ወደ አንድ ግዙፍ ተራራ ሔዱ:: +ሕዝቡ ባንድ ወገን: ከሊፋውና ሠራዊቱ በሌላ ወገን ቆሙ:: ቅዱሳኑ ከምዕመናን ጋር "41 ኪርያላይሶን" አድርሰው: ሰግደው ቀና ሲሉ ተራራው ተነቅሎ በዓየር ላይ ተንሳፈፈ:: ለማጽናትም 3 ጊዜ ተነቅሎ ተተከለ:: +በሁዋላም ወደ ሌላ ቦታ አልፎ ተቀመጠ:: በዚህች ዕለትም በድንግል ምልጃ: በቅዱሳኑ ጸሎት ታላቅ ሞገስ ሆነ:: ወዲያው ግን ቅዱስ ስምዖን ተሰወረ:: ውዳሴ ከንቱን ይጠላልና:: አባ አብርሃምም በቀሪ ዘመኑ ተግቶ ዐርፏል:: ዛሬ የ2ቱም መታሰቢያ ነው:: +ሊቃውንትም ቅዱስ ስምዖንን ሲያደንቁ:- "ሰላም ለስምዖን በአፈ ማርያም ዘተአምረ:: እንበይነ ትዕዛዙ ለወልዳ ከመ ዐይኖ አዖረ:: ኢይሌብውዎ ሎቱ ወኢይጸግውዎ ክብረ:: ሶበ ጸለየ ቀዊሞ ለሊቀ ዻዻሳት ድኅረ:: ነቀለ ደብረ ወተከለ ደብረ" ብለዋል:: (አርኬ) =>አምላከ ቅዱሳን ተራራ ያፈለሱበትን እምነታቸውን አይንሳን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን:: =>ታሕሳስ 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት= 1.ቅድስት አርሴማ ድንግል 2."119" ሰማዕታት (ማሕበሯ) 3.ቅዱስ ስምዖን ጻድቅ (ጫማ ሠፊው) 4.አባ አብርሃም ሶርያዊ 5.ቅዱስ እንጣልዮስ ሰማዕት ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም 2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን 3.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል 4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ 5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ 6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ 7.ቅድስት ሰሎሜ 8.አባ አርከ ሥሉስ 9.አባ ጽጌ ድንግል =>+"+ እውነት እላቹሃለሁ:: የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ ይህን ተራራ ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል:: የሚሳናችሁም ነገር የለም:: +"+ (ማቴ. 17:20) ✞✞✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞✞✞
Mostrar todo...
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞ ✞✞✞ ታኅሣሥ 6 ✞✞✞ ✞✞✞ እንኩዋን "ለድንግልና ሰማዕት ቅድስት አርሴማ" : "አባ አብርሃም" እና "ቅዱስ ስምዖን ጫማ ሰፊው" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞ +*" ቅድስት አርሴማ ድንግል "*+ =>እናታችን ቅድስት አርሴማን በምን እንመስላታለን? እርሷ በአድማስ ላይ ተቀምጦ እንደሚያበራ እንቁ ናትና ክብሯ ብዙ ነው:: መድኃኒታችን ክርስቶስ በወንጌል እንዳለው "በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትምና" (ማቴ. 5:11) የሰማዕቷ ሕይወት በፊታችን እንደ ብርሃን ተገልጦ ይታያል:: *ቅድስት አርሴማ እንደ ልጅ ወላጆቿን በመታዘዝ ደስ ያሰኘች ቡርክት ናት:: *ቅድስት አርሴማ ይሕ ቀረሽ የማይሏት ውብ ናት:: *ቅድስት አርሴማ ድንግል ናት:: *ቅድስት አርሴማ ባሕታዊት ጻድቅ ናት:: *ቅድስት አርሴማ ኃያል ሰማዕት ናት:: ¤ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ: +አበው በትውፊት እንደ ነገሩን ከሆነ ቅዱሱ ጐርጐርዮስ የታላቁዋ ሰማዕት ቅድስት አርሴማ ትልቅ ወንድም ነው:: በዜና ሰማዕታት ተጽፎ እንደሚገኘው በዚያ የመከራ ዘመን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሦስት ኃላፊነቶች ነበሩበት:- 1.ቅድስት አርሴማን ጨምሮ ደናግሉን ማጽናት 2.ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ ማጥናት 3.የሚመጣውን መከራ ለመቀበል ራሱን ማዘጋጀት:: +ቅዱሱ 3ቱንም ኃላፊነቶች በሚገባ በመወጣቱ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ አርአያ መሆን ቻለ:: ያቺን ንጽሕት አርበኛ ቅድስት አርሴማንም አጽንቶ የደናግሉ መሪ አደረጋት:: መከራው ገፍቶ እስከ መጣበት ጊዜ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ ሆነው ይጸልዩ: ይጾሙ: ገዳማዊ ሥራንም ይሠሩ ነበር:: +ለዚህም ነው ቅድስት አርሴማና ቅዱስ ጐርጐርዮስ ጻድቃን የምንላቸው:: በሁዋላ ግን ማሕደረ ሰይጣን ዲዮቅልጢያኖስ በመልኩዋ ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ድንግሏን አርሴማን ጨምሮ ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ አርማንያ ተሰደደ:: +በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና በጸሎት ለጥቂት ጊዜ ቆዩ:: ነገር ግን ረሃብ ፈጃቸው:: የሚላስ የሚቀመስ ነገር በአካባቢው ባለ መኖሩ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወደ ከተማ ለመውጣት ተገደደ:: +በዚያም በድርጣድስ ቤተ መንግስት ውስጥ ባርነት ተቀጠረ:: በሚያገኛት ገንዘብም ወገኖቹን ይረዳ ነበር:: መከራው ግን አለቀቃቸውም:: ርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከው:: +ድርጣድስ ግን ቅድስት አርሴማን ባያት ጊዜ ከውበቷ የተነሳ መታገስ ባለመቻሉ "ካላገባሁሽ" አላት:: ድንግሊቱ ግን "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ: አይሆንም" አለችው:: ሊያስፈራራት ሞከረ:: ዐይኗ እያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው:: +አልሳካልህ ቢለው በአደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞክር እጁን ጠምዝዛ በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው:: እጅግ ስላፈረ አስገረፋት: አሰቃያት: ዐይኗንም አወጣ:: በመጨረሻም አንገቷን አስቆርጦ ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት:: +ከነገር ሁሉ በሁዋላ ድርጣድስና ባለሟሎቹ ለአደን በሔዱበት ርኩስ መንፈስ ወደ አውሬነት (እሪያነት) ቀየራቸው:: +የንጉሡ እንስሳ (አውሬ) መሆን በአርማንያ ታላቅ ድንጋጤን ፈጠረ:: የንጉሡ እህት ስታለቅስ በራዕይ "ለእመ ኢያዕረግምዎ ለጐርጐርዮስ አልብክሙ ድኂን-ጐርጐርዮስን ከተቀበረበት ካላወጣችሁት አትድኑም" አላቸው:: ወዲያውም ቆፍረው አወጡት:: +ቅዱሱ እንደ ወጣ ዕረፍትን አልፈለገም:: ለ15 ዓመታት ቀባሪ አጥቶ የተበተነውን የቅድስት አርሴማንና የሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ በክብር አኖረው:: ድርጣድስና ባለሟሎቹንም ወደ በርሃ ሒዶ ፈወሳቸው:: +የሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ አጽም በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን ከሌሎች ሰማዕታት አጽም ጋር ኢትዮዽያ እንደ መጣ አባቶቻችን በትውፊት ነግረውናል:: ለዚህም ይመስላል ቡርክቷ እናታችን ከሌሎች ሃገራት ለይታ ለኢትዮዽያውያን ልዩ ፍቅር ያላት:: በዋናው ገዳሟ (ወሎ /ኩላማሶ/ : ስባ : ውስጥ የሚገኝ ነው) ጨምሮ ስሟ በተራበት ሁሉ ኃይልን ታደርጋለችና:: +ነገር ግን ወንድሞቼና እሕቶቼ በቅድስቷ እናታችን ስም የሚነግዱ ሥጋውያን ሰዎች በዝተዋልና እንጠንቀቅ:: የሰማዕቷ ክብር ብዙ ነውና በሕልም ላይ ብቻ አንታመን:: አባ እንጦንስ እንዳሉት "በሕልሙ የሚታመን ሰው ከንቱ ነውና::" (መዝ. 75:5) +በዚህ ዕለት ከሰማዕቷ ጋር የመንፈስ እናቷን ቅድስት አጋታን ልናስባት ይገባናል:: ይህች እናት እመ-ምኔት ስትሆን ቅድስት አርሴማን ታስተምራት: ታጸናት: ከጐኗም ትቆምላት ነበር:: ረሃቧን: ጥሟን: ስደቷን: መከራዋንም ሁሉ አብራት ተሳትፋለች:: በፍጻሜውም አብራት ተሰይፋለች:: +ይህች ዕለት ለቅድስት አርሴማና ለተከታዮቿ ሰማዕታት የፍሰትና የቅዳሴ ቤት መታሰቢያ ናት:: +"+ አባ አብርሃምና ቅዱስ ስምዖን ጫማ ሰፊው +"+ =>እነዚህ 2 ኮከቦች በ11ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ በምድረ ግብጽ ተነስተው ለቤተ ክርስቲያን ድንቅ ተአምርን የሠሩ አበው ናቸው:: እመ ብርሃን ማርያም ለሥራ እስክታገናኛቸው ድረስም እርስ በርስ አይተዋወቁም ነበር:: +"+ አባ አብርሃም +"+ =>ይህ ቅዱስ ትውልዱ ከሶርያ ሲሆን እጅግ የታወቀ ነጋዴ ነበር:: ከሶርያ ግብጽ እየተመላለሰ ሲነግድ ባለ ጸጋ ሆኖም ነበር:: ነገር ግን ክርስትናን አጥብቆ የተማረ: ነዳያንን የማይዘነጋ: ጾምና ጸሎትን የማይገፋና እኔን ብቻ ይድላኝ የሚል ሰው ስላልነበረ እግዚአብሔር ለታላቅ ሥራ ጠራው:: +የግብጽ 61ኛ ፓትርያርክ አባ ፊላታዎስ ባረፈ ጊዜ አበው ተተኪ ፍለጋ ሱባኤ ቢገቡ "ሶርያዊ አብርሃምን ሹሙ" አላቸው:: እርሱ "እንቢ" ቢልም አለቀቁትም:: እርሱም ከሆነስ ብሎ ሃብቱን እኩሉን ለነዳያን: እኩሉን ለገዳማት ሰጥቶ ባዶ እጁን ወደ መንበረ ዽዽስናው ወጥቷል:: በዘመነ ሲመቱም ልማደ ኃጢአትን ያርቅ ዘንድ ብዙ ተግቷል:: +"+ ቅዱስ ስምዖን ሰፋዪ +"+ =>በዚያው ዘመን በምስር (በአሁኗ CAIRO) አካባቢ ራሱን ደብቆ: ጫማ እየጠገነ: ነዳያንን እየመገበ: ድኩማንን እየረዳ: በፍጹም ትሕትና: በጾምና በጸሎት የኖረ አባት ነው:: አንዲት ወጣት ልታስተው ብትመጣም ስለ ክርስቶስ ትዕዛዝ አንድ ዐይኑን በመሳፈቻ አውጥቶ ጥሏል:: +"+ በእምነት ተራራ ሲነቀል +"+ =>በወቅቱ የነበረው የግብጽ ከሊፋ ፍልስፍና ወዳጅ በመሆኑ ምሁራንን ያከራክር ነበር:: አንድ አይሁዳዊ "ምሑር" ነኝ ባይም ከክርስቲያኖች ጋር መከራከር ፈልጐ ጠየቀ:: አባ አብርሃምና አባ ሳዊሮስ መጥተው ድል ነስተው: አሳፍረውት ሔዱ:: +እርሱም በቂም በማቴ. 17:20 ላይ ያለችውን ቃል ይዞ ሒዶ በከሊፋው ፊት አቀረበ:: ቃሉም:- "የሰናፍጭ ቅንጣት ታሕል እምነት ቢኖራችሁ ይህንን ተራራ ተነቀል . . . ብትሉት ይቻላቹሃል" ይላል:: +ከሊፋውም አባ አብርሃምን ጠርቶ "መጽሐፍ ቅዱሳችሁ እንደዚህ ይላል?" አለው:: "አዎ!" ሲል መለሰለት:: "አድርገህ አሳየኝ" ቢለው 3 ቀናትን ለምኖት ወጣ:: ሁሉም ክርስቲያኖች የ3 ቀን ምሕላ ሲይዙ አባ አብርሃም በእመቤታችን መቅደስ ለ3 ቀናት ያለ ምግብና እንቅልፍ አለቀሰ::
Mostrar todo...
✝እንኳን አደረሰነ! ✞በዓለ ቅዱሳን፦ ✿ናሆም ነቢይ (ፈዋሲ) ✿አውጋንያ ተጋዳሊት (ዘሮሜ) ✿ፊቅጦር ሰማዕት (ዘሻው) ✿ገብረ ናዝራዊ (ንጹሕ ወድንግል) ✿አኖሬዎስ ንዑስ (ዘወግዳ) ✿ፊልጶስ ወዮሐንስ ✿ሐናንያ ወባርክዮስ ✿ኤላውትሮስ ወኤስድሮስ ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ በረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡ https://t.me/zikirekdusn
Mostrar todo...
✞✞✞Saint Victor of Shaou (Shaw)✞✞✞=>This Saint is one of the great martyrs. And Shaou is the place where he was martyred. The Saint is also known as Victor ll. He lived, persisting in goodness, in the upright way that he inherited from his Christian parents.   ✞Though he was a youth, a leader of a region, rich and handsome, all of them were not able to separate him from the love of Christ. (Rom. 8:35) And when the Era of Persecution came, shunning his honor, he received affliction for the sake of Christ and on this day was martyred with his followers. And the Lord has given him a covenant. ✞✞✞May the God of the Saints not conceal from us the mystery of sanctity of His beloved. And may He multiply their blessings for us. ✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 5th of Tahisas 1. St. Eugenia the Fighter 2. Abba Gebre Nazrawi the Pure (Ethiopian) 3. St. Victor the Martyr (Of the City of Shaou /Shaw) 4. St. Philip the Martyr (St. Eugenia’s Father) 5. St. Nahum the Prophet  ✞✞✞ Monthly Feasts 1. St. Peter, Arch-Apostle (First among the Apostles) 2. St. Paul, Light of the World 3. Abune Gebre Menfes Qidus 4. St. Yohani the Ethiopian 5. St. Amoni of Nah(i)so ✞✞✞ “. . . but yet I would have you wise unto that which is good, and simple concerning evil. And the God of peace shall bruise Satan under your feet shortly. The grace of our Lord Jesus Christ be with you. Amen.”✞✞✞ Rom.16:19-20 ✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞ (Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
Mostrar todo...
Nonetheless, because the choice was by the Holy Spirit, they insisted and she was appointed as a shepherd upon all those monks.✞Of course, she was a woman and a youthful one at that but because she truly loved Christ, she administered the monks in complete diligence. And because the grace of God was abundant in her, she used to console the anxious and used to heal with her prayers by laying her hands upon the sick. And by this, the monks were gladdened.     ✞She in turn used to pass through many trials. Because her name was famed beyond the desert and entered the cities, the sick used to come to her and were made whole. Nevertheless, one day an unexpected trial came her way. ✞One Satan possessed woman, after she healed her, because her appearance was very beautiful asked her for adultery (the woman asked the woman) as she thought that she was a man. However, St Eugenia rebuked her and sent her on her way. And that wicked young lady, who was upset, went to the city and accused her to the governor Philip (who was the Saint’s father).  ✞Her father (Philip) since the day the Saint had went missing had an idol built in her name and used to prostrate before it. And because that youth had accused her falsely saying, “The monks in the monastery, particularly the one they call Eugenius, their leader, when he tried to rape me I escaped” Philip ordered that the monastery be raided and the monks lashed. ✞During the lashings many monks died. And St. Eugenia who was enraged by the torments that the monks were enduring took her father to a private place and revealed who she was. And when he found his daughter that he missed, in jubilation he ordered that they leave the monks alone.  ✞And seating with his daughter in private, she told him all the things that had happened and explained to him about the heavenly life. She then broke the idol that was created in her name and then had her father baptized. He also became an ascetic and lived for many years. Then, he was appointed a bishop. ✞And on this day, he was beheaded for the sake of Christ. But St. Eugenia went from Egypt to Rome and established a convent for virgins. And under her, God gathered 3,300 virgins. And after she lived consoling, counseling and leading them for years, the ruler of the region asked her to renounce her faith. ✞And because she said, “No” like her father, she was beheaded and became a martyr. The 2 eunuchs that had become ascetics with her also became bishops and did serve the Church. ✞✞✞Honor is due to our mother St. Eugenia who is a virgin, an ascetic, a healer, a consoler, an abbot, an abbess, a righteous and a martyr. ✞✞✞ Abba Gebre Nazrawi✞✞✞ =>This Saint was an Ethiopian that lived in the 14th century. He is well known in Tigray (where his monastery is) and around Shewa. The father who tonsured him a monk, Abba Gorgorios (Gregory), was the disciple of the Great Abba Anorios (Honorius) of Debre Tsegaga. ✞Abba Gebre Nazrawi after he struggled in different monasteries, by the council of the elders he establish his own monastery. He then gathered many disciples and the monastery became great. At the time, it had become a monastery with strict rules next only to the Monastery of Wali (Waldiba). ✞And the reason for it was because Abba Gebre Nazrawi was a completely austere father and did not allow any monk to eat except one meal a day. And next to Abune Ewostatewos the Saint takes a huge place in honoring and having the Sabbath honored. ✞Chiefly, he has fought for Saturday to be revered. And because he was a good abbot, he has bore many righteous fathers for our country. And he used to be jubilant in the Psalms of David for 24 hours without consuming a cooked meal. ✞And he used to prostrate until his sweat dripped. And to fulfill the apostolic deed, while he preached the Gospel, he used to give as alms what he had. Today is the day the Saint departed.
Mostrar todo...
Memhir Esuendale: #Feasts of #Tahisas_5 ✞✞✞On this day we commemorate Saint Eugenia, Abba Gebre Nazrawi and Saint Victor of Shaou (Shaw)✞✞✞ ✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞ ✞✞✞Saint Eugenia✞✞✞ =>The invocation of this Holy Youth’s name is revered. When her account is heard, it grants a fragrant soul. Hence, let me start [her chronicle] with the aid of God. And you, follow me with the help of God.   ✞St. Eugenia was a fruit of 3rd century Christianity. She was Roman in lineage and her father was called Philip. He was a commander and a governor. And her mother who is not mentioned by name (though some say Klothia) was a Christian. ✞And as the time was hostile to Christians; she hid her Christianity and lived like a heathen. However, when she gave birth to St. Eugenia, she was vexed as the lot of her daughter and herself was going to be death if she had her baptized. ✞And that was because Philip was an idol worshipper that utterly hated Christianity. And beyond that, he used to force people to kneel and bow down to idols. Thus, the mother raised her child with a whole Christian teaching and manner but without having her baptized. ✞Thereafter, St. Eugenia became a youth that was infused with fasting, prayer, humility and patience. Nevertheless, she used to daily beseech her Creator so that she could receive the mystery of baptism.  ✞And while they were in this situation, one fortunate event took place. Because her father, Philip, was appointed as a duke for Alexandria in the Land of Egypt, they took all their possessions and left. Though this was a good fortune for St. Eugenia, it brought her another trial.   ✞She heard that her father was going to wed her to a heathen official. At that time, because it was necessary to resolve, she made a decision. She then went to her father and asked, “Father! Do this one thing for me. Thereafter, I will obey whatever you will say. However, give me permission so that I could go to the wilderness to see the sights and come back before my wedding day.” ✞And her father, who did not suspect anything, sent her with 2 eunuchs (named as Protus and Hyacinth). And when they reached the desert, St. Eugenia told her attendants, the 2 eunuchs, the truth. ✞She said, “I am going to the desert to become a Christian and then to become an ascetic. Hence, if you do not want that, return.” Yet, both of them said, “Our life and death is with you” and entered together into a monastery. ✞And when they reached there, she told their secret to a righteous monk (Theodore while some say Helenus, bishop of Heliopolis) and asked him to baptize her. Then, after the monk baptized all 3, St. Eugenia said, “Make me a nun” and he replied, “My child! This is a monastery for men.” ✞But she reiterated, “Father! That is no problem! I will conceal myself.” Then, he taught her the rites of a monastery and tonsured her a monk, naming her “Abba Eugenius” and added her to the brethren. Feminine names like Eugenia, Theodora, Anastasia . . . and the like can easily be changed to masculine ones like Eugenius, Theodore, Anastasias. ✞And from that day onwards St. Eugenia began her strife as Abba Eugenius. During the day, she used to do the hard work, which the monks did, and in the night, she used to pray diligently. And for one year she served the monastery in complete attentiveness. ✞And she endured the trials that came to her all through that time as Christ, for Whose sake she shunned the world and left her father’s palace for, was her power/strength. And at that moment, since the Abbot had passed away, the monks fasted and prayed for some time to choose the next Abbot who could lead the monks and give confessions. ✞After they completed their fast and gathered, the message they received form the Holy Spirit was astounding. All their eyes laid on Abba Eugenius. However, she knowing her secret (her womanhood), was shocked.
Mostrar todo...
+ለዚህም ምክንያቱ አባ ገብረ ናዝራዊ ፍጹም ተሐራሚ በመሆናቸው ማንኛውም መነኮስ ከአንድ ማዕድ ውጪ እንዲቀምስ የማይፈቅዱ ስለ ነበር ነው:: ከታላቁ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ቀጥሎም ሰንበትን አክብሮ በማስከበር ጻድቁ ትልቁን ቦታ ይይዛሉ::+በተለይ ቀዳሚት ሰንበት እንድትከበር ታግለዋል:: በበጐ አበ_ምኔትነታቸውም ብዙ ፍጹማንን ለሃገራችን አፍርተዋል:: ራሳቸው የበሰለ ነገር ወደ አፋቸው ሳያስገቡ 24 ሰዓት በዳዊት መዝሙር ይደሰቱ ነበር:: +ላባቸው እስኪንጠፈጠፍም ይሰግዱ ነበር:: ሐዋርያዊ ግብርን ለመፈጸምም ወንጌልን እየሰበኩ ያለቻቸውን ነገር ይመጸውቱ ነበር:: ዛሬ የጻድቁ ዕረፍታቸው ነው:: +"+ ቅዱስ ፊቅጦር ዘሻው +"+ =>ይህ ቅዱስ ከታላላቅ ሰማዕታት አንዱ ነው:: ሻው ማለት ሰማዕትነትን የተቀበለባት ቦታ ስትሆን "ፊቅጦር ካልዕም" ይባላል:: ከክርስቲያን ወላጆቹ የወረሰውን በጐነት አጽንቶ በቅን መንገድ ኑሯል:: +ምንም ወጣት: የሃገር አስተዳዳሪ: ሃብታምና መልከ መልካም ቢሆንም ይህ ሁሉ ከክርስቶስ ፍቅር ሊለየው አልቻለም:: (ሮሜ. 8:35) ዘመነ ሰማዕታት በደረሰ ጊዜም ክብሩን ንቆ: ስለ ክርስትና ብዙተ ሰቃይቶ: በዚህች ቀን ከነ ተከታዮቹ ሰማዕት ሆኗል:: ጌታም ቃል ኪዳንን ገብቶለታል:: =>አምላከ ቅዱሳን የወዳጆቹን ምሥጢረ ቅድስና አይሰውርብን:: በረከታቸውንም ያብዛልን:: =>ታሕሳስ 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት= 1.ቅድስት አውጋንያ ተጋዳሊት 2.አባ ገብረ ናዝራዊ ንጹሕ 3.ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት 4.ቅዱስ ፊልዾስ ሰማዕት 5.ቅዱስ ናሆም ነቢይ ወርኀዊ የቅዱሳን  በዓላት 1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት 2.ቅዱስ ዻውሎስ ብርሃነ ዓለም 3.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ 4.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ 5.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ =>+"+ ነገር ግን ለበጐ ነገር ጥበበኞች: ለክፉትም የዋሆች እንድትሆኑ እወዳለሁ:: የሰላምም አምላክ ሰይጣንን ከእግራችሁ በታች ፈጥኖ ይቀጠቅጠዋል:: የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን:: +"+ (ሮሜ. 16:19) ✞✞✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞✞✞
Mostrar todo...
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞ ✞✞✞ እንኩዋን ለእናታችን "ቅድስት አውጋንያ" : "አባ ገብረ ናዝራዊ" እና "ቅዱስ ፊቅጦር" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞ +*" ቅድስት አውጋንያ "*+ =>ይህቺ ቅድስት ወጣት ስም አጠራሯ በእውነት የከበረ ነው:: ዜና ሕይወቷ ሲሰማ ጣዕመ ነፍስን ያድሳልና:: በፈጣሪ ረዳትነት ልጀምር:: እናንተም በእግዚአብሔር አጋዥነት ተከተሉኝ:: +ቅድስት አውጋንያ የ3ኛው መቶ ክ/ዘ የክርስትና ፍሬ ናት:: በትውልዷ ሮማዊት ስትሆን አባቷ ፊልዾስ ይባላል:: ሥራውም የጦር መሪ: የሃገርም አስተዳዳሪ ነው:: በስም ያልተጠቀሰች እናቷ ደግሞ ክርስቲያን ነበረች:: +ዘመኑ አስከፊ ሰለ ነበር (ለክርስቲያኖች ማለቴ ነው) ክርስትናዋን ደብቃ: አልባሌ (አሕዛባዊ) መስላ ትኖር ነበር:: ቅድስት አውጋንያን ስትወልድ ግን ጨነቃት:: እንዳታስጠምቃት የእርሷም ሆነ የሕጻን ልጇ እጣ ፈንታ ሞት መሆኑ ነው:: +ምክንያቱም ባሏ ፊልዾስ ክርስትናን ፈጽሞ የሚጠላ ጣዖት አምላኪ ነበርና:: ከዚያም አልፎ ሰዎች ለጣዖት እንዲንበረከኩም ያስገድድ ነበር:: ስለዚህ እናት ልጇን ሳታስጠምቅ: ግን በፍጹም የክርስትና ትምሕርትና ሥርዓት አሳደገቻት:: +ቅድስት አውጋንያም ጾምን ጸሎትን: ትሕትናን: ትእግስትን የተመላች ወጣት ሆነች:: ግን ምሥጢረ ጥምቀትን ታገኝ ዘንድ ዘወትር ፈጣሪዋን ትማጸን ነበር:: +በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉም አንድ መልካም አጋጣሚ ተፈጠረ:: መኮንኑ አባቷ (ፊልዾስ) በምድረ ግብጽ እስክንድርያ አገረ ገዥ ሆኖ በመሾሙ ጉዋዛቸውን ጠቅልለው ወረዱ:: ምንም ይህ ለቅድስት አውጋንያ መልካም አጋጣሚ ቢሆንም ሌላ ፈተናን አመጣባት:: +አባቷ ለአረማዊ መኮንን ሊድራት መሆኑን ሰማች:: አሁን ግን መቁረጥ ያስፈልግ ነበርና ወሰነች:: ወደ አባቷ ገብታም "አባቴ! አንድ ነገር ላስቸግርህ:: አንተ ለምትለኝ ሁሉ እታዘዛለሁ:: ግን ከሠርጌ ቀን በፊት ለአንዲት ቀን በዱር ውስጥ ተናፍሼ: ተዝናንቼ እንድመጣ ፍቀድልኝ?" አለችው:: +ምን እንዳሰበች ያልጠረጠረ አባቷም ከ2 ጃንደረቦች ጋር እንድትሔድ አደረገ:: በርሃ አካባቢ ሲደርሱም ቅድስት አውጋንያ እውነቱን ለ2ቱ ጃንደረቦች ተከታዮቿ ነገረቻቸው:: +"እኔ ወደ በርሃ የምሔደው ክርስቲያን ልሆን: ደግሞም ልመንን ነውና ካላሰኛችሁ ተመለሱ" አለቻቸው:: 2ቱም ግን በአንድ ቃል "ሞታችንም: ሕይወታችንም ከአንቺ ጋር ነው" ብለዋት አብረው ገዳም ገቡ:: +እንደ ደረሱም ምሥጢራቸውን ለአንድ ጻድቅ መነኮስ ተናግራ እንዲያጠምቃት ጠየቀችው:: መነኮሱም 3ቱንም ካጠመቃቸው በሁዋላ ቅድስት አውጋንያ "አመንኩሰን" ብትለው "ልጄ! ይሔ የወንዶች ገዳም ነውኮ" አላት:: +"አባ! ግድ የለህም! እኔ ራሴን እሰውራለሁ" አለችው:: ከዚያም ሥርዓተ ገዳምን አስተምሮ ስሟን "አባ አውጋንዮስ" ብሎ ከማሕበረ መነኮሳቱ ቀላቀላት:: *አውጋንያን *ታኦድራ *አንስጣስያ . . . የመሳሰሉ ስሞች በቀላል መንገድ ወደ ወንድ ስምነት *አውጋንዮስ *ቴዎድሮስ *አንስጣስዮስ . . .በሚል መቀየር ይችላሉና:: +ከዚህች ዕለት ጀምራ ቅድስት አውጋንያ በአባ አውጋንዮስነቷ ተጋድሎን ጀመረች:: ቀን ቀን ወንዶች መነኮሳት የሚሠሩትን ከባድ ሥራ ሁሉ ስትሠራ ትውልና ሌሊት በትጋት ስትጸልይ ታድራለች:: ለ1 ዓመት ያህል በፍጹም ተጸምዶ ገዳሙን አገለገለች:: +በነዚህ ጊዜያት የመጡባትን ፈተናዎችም ታገሰች:: ዓለምን የናቀችለት: የአባቷን ቤተ መንግስት የተወችለት ክርስቶስ ኃይሏ ነበርና:: በዚያ ሰሞንም የገዳሙ አበ ምኔት በማረፉ መነኮሳትን የሚመራና የሚናዝዝ ሌላ አበ ምኔትን ለመምረጥ ሱባኤ ገቡ:: +ከሱባኤ ወጥተው ሲሰበሰቡ ግን ያመጡት የመንፈስ ቅዱስ መልእክት የሚገርም ነበር:: የሁሉም ዓይን ወደ አባ አውጋንዮስ ተወረወረ:: እርሷ ምሥጢሯን (ሴትነቷን) ታውቃለችና ደነገጠች:: ምርጫው ግን የመንፈስ ቅዱስ ነበርና ግድ ብለው በእነዛ ሁሉ መነኮሳት ላይ እረኛ ሁና ተሾመች:: +በእርግጥ እርሷ ሴት በዚያውም ላይ ወጣት ናት:: ግን እውነተኛ የክርስቶስ ወዳጅ ነበረችና በፍጹም ትጋት መነኮሳትን አስተዳደረች:: ጸጋው ቢበዛላት የተጨነቀውን ታረጋጋ: የታመመውን እጇን እየጫነች በጸሎቷ ትፈውስ ነበር:: በዚህም መነኮሳቱ ደስ ተሰኙ:: +እርሷ ግን ስለዚህ ፈንታ ብዙ ፈተናዎችን በአኮቴት ታሳልፍ ነበር:: ስም አጠራሯም ከበርሃ ወጥቶ ወደ ከተሞች በመግባቱ ድውያን እየመጡ ከእርሷ ዘንድ ይፈወሱ ነበር:: አንድ ቀን ግን ያልተጠበቀ ፈተና መጣባት:: +አንዲት ሰይጣን ያደረባትን ሴት ካዳነቻት በሁዋላ: መልኩዋ እጅግ ውብ ስለ ነበር የዝሙት ጥያቄን አቀረበችላት:: (ሴቷ ለሴቷ ማለት ነው) ለእርሷ ወንድ መስላታለችና:: ቅድስት አውጋንያ ግን ገሥጻ ሰደደቻት:: በዚህ የበሸቀችው ያቺ ክፉ ወጣት ወደ ከተማ ሒዳ ለሃገረ ገዢው ፊልዾስ (የቅድስቷ አባት) ክስ አቀረበች:: +እርሱ (ፊልዾስ) አውጋንያ ከጠፋችበት ቀን ጀምሮ በስሟ ጣዖት አሠርቶ የሚሰግድ ሆኖ ነበር:: ወጣቷ "በገዳም ያሉ መነኮሳት: በተለይ አውጋንዮስ የሚሉት መሪያቸው አስገድዶ ከክብር ሊያጐድሉኝ ሲሉ አመለጥኩ" ብላ በሃሰት በመክሰሷ ገዳሙ እንዲመዘበር: መነኮሳቱም እንዲገረፉ መኮንኑ ፊልዾስ አዘዘ:: +በግርፋቱ መካከልም ብዙ መነኮሳት ሞቱ:: የእነርሱ ስቃይ ያንገበገባት ቅድስት አውጋንያ ግን አባቷን ለብቻ ወስዳ አስምላ ማንነቷን ገለጸችለት:: የናፈቃት ልጁን ሲያገኝ ደስ ብሎት መነኮሳቱን እንዲተዉ አዘዘ:: +ለብቻ ከልጁ ጋር ተቀምጦም ያለፈውን ነገር ሁሉ ነግራ ስለ ሰማያዊ ሕይወት አስረዳችው:: በስሟ የተቀረጸውን ጣዖትም ሰብራ አባቷን አስጠመቀችው:: እርሱም መንኖ ለዓመታት ኖረ:: ከዚያም ዻዻስ ሆኖ ተሹሟል:: +በዚህች ቀንም ስለ ክርስቶስ አንገቱን ተሰይፏል:: ቅድስት አውጋንያ ግን ከግብጽ ወደ ሮም ሒዳ የደናግል ገዳምን መሠረተች:: በሥሯም አምላክ 3,300 ደናግልን ሰበሰበላት:: እነርሱን ስታጽናና: ስትመክር: ስትመራ ለዓመታት ኑራ በአካባቢው ገዢ ሃይማኖቷን እንድትክድ ተጠየቀች:: +"እንቢ" በማለቷ እርሷም እንደ አባቷ በዚህች ቀን ተሰይፋ ሰማዕት ሆናለች:: አብረዋት የመነኑ 2ቱ ጃንደረቦችም ዻዻሳት ሆነው ቤተ ክርስቲያንን አገልግለዋል:: << *ድንግል: *መናኝ: *ፈዋሽ: *ናዛዥ: *አበ ምኔት: *እመ ምኔት: *ጻድቅትና *ሰማዕት ለሆነች ለእናታችን ቅድስት አውጋንያ ክብር ይገባል! >> +"+ አባ ገብረ ናዝራዊ +"+ =>እኒህ ጻድቅ በ14ኛው መቶ ክ/ዘ የነበሩ ኢትዮዽያዊ ናቸው:: ጻድቁ ትግራይ (ገዳማቸው ያለበትና) ሽዋ አካባቢ በደንብ ይታወቃሉ:: የእርሳቸው የቆብ አባት የሆኑት አባ ጐርጐርዮስ የታላቁ አኖሬዎስ (የደብረ ጽጋጋው) ልጅ ናቸው:: +አባ ገብረ ናዝራዊ በምናኔ በየገዳማቱ ሲጋደሉ ከኖሩ በሁዋላ በምክረ አበው ራሳቸው ገዳምን መሥርተዋል:: ብዙ ደቀ መዛሙርትንም ሰብስበው ገዳሙ ታላቅ ሆኗል:: በወቅቱ ከገዳመ ዋሊ (ዋልድባ) ቀጥሎ ጥብቅ ሥርዓት የነበረበት ታላቅ ገዳምም ሆኖ ነበር::
Mostrar todo...
ታቦት ዘዶር (የብርሃን ማደሪያ).m4a82.79 MB
ድንግል ማርያምን እናመስግናት.m4a49.18 MB
1:05:20
Video unavailableShow in Telegram
✝እንኳን አደረሳችሁ ! ✞በዓታ ለማርያም ድንግል (ውስተ ቤተ መቅደስ) ✞ቅዱስ ፋኑኤል (ሊቀ መላእክት) ✞አቡነ ዜና ማርቆስ (ዘደብረ ብሥራት) ✞ኢያቄም ወሐና፥ ዘካርያስ ወስምዖን ☞አዕርፍ ነፍሰ አቡነ ሣሕለ ማርያም! https://t.me/zikirekdusn
Mostrar todo...
89.98 MB