ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
Ir al canal en Telegram
በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
Mostrar más2025 año en números

50 489
Suscriptores
+1024 horas
+37 días
+11030 días
Archivo de publicaciones
However, because she had to discuss with her children, they sat to converse. Then, three of her children chose asceticism which they had longed for since their childhood.
✞And per their choice, St. Theodata sent Saints Anthimus, Leontius (Londius), and Euprepius (Abrabius) on their way to the desert with a blessing. And she remained with her two holy sons, Cosmas and Damian.
✞And these Saints stayed in the city not because they wished for the world. Rather they stayed there to serve the Saints of God that were receiving affliction in prison.
✞While St. Theodata fed and received the destitute at her home, the two Saints, her sons, on the other hand spent the day going around the city visiting, consoling, washing the wounds of, and feeding the imprisoned (imprisoned for the sake of Christ).
✞Though, this - their deed, delighted their Creator, it greatly angered Diocletian the Beast. He immediately ordered that they be caught and brought before him. Accordingly, Cosmas and Damian were brought before him chained.
✞He then said, ”How dare you disrespect my orders! Again, choose between torture and death or obeying my orders.” Thus, the choice of the Saints was clear as there was no power that could separate them from the love of Christ. (Rom. 8:36)
✞And the Emperor ordered saying, “Lash them.” Thus, they removed their clothes, tied them upside down and beat them with metal and wooden rods. And their blood dripped on the ground. However, they were praising God.
✞And because this news had reached St. Theodata, their mother, she hastily came to the square of the martyrs. And what a mother feels when she sees her children hanged in public and their blood dripping is only known by one who had encountered it as well.
✞Nevertheless, she was reassured when she thought about their honor. And speedily, amid the people, she rebuked the apostate boldly regarding his ignorance. And the Emperor in anger had her beheaded. The two Saints saw this and wished for one thing, a person who would entomb the body of their mother.
✞However, because all were afraid, the body of the Saint laid on the ground for a whole day. And at that juncture, St. Cosmas screamed loudly in grief, “Is there no one amongst you that would show a little compassion to this elderly woman?” And suddenly the great military commander St. Victor arrived at the scene.
✞While carrying his sword, he entered the midst and took up the Saint’s body. And carrying her honorably, he buried her. Finally, because the news of their three brothers was heard as well, they were caught and brought to the city by soldiers. Thereafter, after afflicting them with much tortures, their oppressors lined the five up and killed them on this day. And the Martyrs received glory upon glory with their mother.
✞✞✞May the God of the Martyrs grant us from their patience, persistence, and blessings.
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 22nd of Hedar
1. Saints Cosmas and Damian (Martyrs)
2. Saint Theodata (Their mother)
3. Saints Anthimus, Leontius (Londius), and Euprepius (Abrabius) (Their brothers)
4. The “311” Martyrs (Followers of Cosmas and Damian)
✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Uriel Archangel
2. St. Dekesius (Devotee of our Lady)
3. Abba Anthony Father of the Monks
4. Abba Paul the Simple
5. St. Julius Martyr
6. St Luke the Evangelist and Apostle
✞✞✞“Ye are of God, little children, and have overcome them: because greater is he that is in you, than he that is in the world. They are of the world: therefore speak they of the world, and the world heareth them. We are of God: he that knoweth God heareth us; he that is not of God heareth not us.”✞✞✞
1 John 4:4-6
✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞
(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
#Feasts of #Hedar_22
✞✞✞On this day we commemorate the Martyrdom of Saints Cosmas and Damian✞✞✞
✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞
✞✞✞ Saints Cosmas and Damian✞✞✞
=>Let us see a bit today the relation of Christianity and youthfulness basing the lives of these blessed Christian brothers. Prior to this, we have heard the accounts of several young martyrs. As Holy Writ states, “For whatsoever things were written aforetime were written for our learning” (Rom. 15:4) we should take notice.
✞✞✞The accounts of the saints are told to us not that we listen to them as stories and pass. Rather,
1. The account of the Saint gives blessing to the person that listens or reads it wholeheartedly.
2. By faith one can partake from the Saint’s covenant (that he/she has received from God).
3. And we learn the ways in which the saints preserved their Christianity, kept It and were able to garner heavenly honor. And the greatest benefit we receive is this.
✞A number of us, the children of Tewahedo (the Faith), either start and stop the lives of the saints as temporal history or read it in a careless manner. And when we favor their icons we place the like button (in social medias) and pass.
✞And sometimes, we read it carefully and pass on admiring with, “How fortunate!” It is good that we admired them, however the saints reached this point not only because they were fortunate rather because they did what was expected of them accordingly.
✞God does not favor one over the other. And He said “Be ye holy; for I am holy”(Lev. 19:2, 1Pet. 1:15) not to a few selected or unique people rather to all those that believe in His name.
✞Hence, us Christians, particularly the youths, should take the proper courses and persist, become strong and should say, “We are here” for the Church. Today, predominantly, in the cities, the Church is becoming barren though she has given birth.
✞It is said that the Church has this and that million Sunday school students and youths. Nonetheless, when properly examined, it is shameful to speak how many out of a hundred are found at the right place. What has happened has happened, but when we ask regarding the solution. [It seems to be the following] Let us learn from early Christian saints what we must do, integrate that with the present era, and let us support ourselves, our church and our country. And let us come out of the ravine of indolence. And for this may God help us to have a committed heart. Now let us pass to the accounts of the Saints (Martyrs).
✞Saints Cosmas and Damian were Christians of the 3rd century A.D that were born and raised in the land of Syria. Because their father departed while they were kids, the burden of raising 5 children fell on their mother. Their mother was called Saint Theodata.
✞She was an amazing, blessed mother. And her five children were called, “Cosmas, Damian, Anthimus, Euprepius (Abrabius), and Leontius (Londius)”. It is obvious that the first concern of a mother in such a situation is “What will my children eat?” However, this was not the main apprehension for St. Theodata.
✞As our Lord had taught us, “take no thought, saying, What shall we eat? or, What shall we drink? or, Wherewithal shall we be clothed?,” she was always worried about her children’s heavenly citizenhood. (Matt. 6:31)
✞And for that reason, she used to take her children daily to the House of God, have them hear His Holy Word, and practice the spiritual life. As God wants from us our good will and a bit of sincere effort, St. Theodata succeeded. Her children grew up in physique and spiritual life.
✞But the era was not like today, rather it was a time when being a Christian was a death sentence. As we have seen in previous similar stories, 275 years after the birth of Christ, the two beasts (Diocletian and Maximian) that ruled Syria and Rome started persecuting Christians and did not allow them to stay in one place.✞And St. Theodata, who succeeded in the first trial, was not fearful to face this head on.
††† ኅዳር 22 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱሳን ቆዝሞስ ወድምያኖስ (ሰማዕታት)
2.ቅድስት ቴዎዳዳ (እናታቸው)
3.ቅዱሳን አንቲቆስ: ዮንዲኖስና አብራንዮስ (ወንድሞቻቸው)
4."311" ሰማዕታት (የነ ቆዝሞስ ማኅበር)
††† ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዑራኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ደቅስዮስ (የእመቤታችን ወዳጅ)
3.አባ እንጦንስ አበ መነኮሳት
4.አባ ጳውሊ የዋህ
5.ቅዱስ ዮልዮስ ሰማዕት
6.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ሐዋርያ
††† "ልጆች ሆይ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ:: አሸንፋችሁአቸውማል:: በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና:: እነርሱ ከዓለም ናቸው:: ስለዚህ ከዓለም የሆነውን ይናገራሉ:: ዓለሙም ይሰማቸዋል:: እኛ ከእግዚአብሔር ነን:: እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል:: ከእግዚአብሔር ያልሆነ አይሰማንም::" †††
(፩ዮሐ. ፬፥፬)
††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
††† እንኳን ለቅዱሳን ሰማዕታት ቆዝሞስና ድምያኖስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††
††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††
††† ቅዱሳን ቆዝሞስ ወድምያኖስ †††
††† እስኪ ዛሬ ስለ ክርስትናና ወጣትነት እነዚህን ቡሩካን ወንድማማች ክርስቲያኖች መሠረት አድርገን ጥቂት እንመልከት:: ከዚህ በፊት የበርካታ ወጣት ሰማዕታትን ዜና ሰምተናል:: መጽሐፍ እንደሚል "ወኩሉ ዘተጽሕፈ ለተግሣጸ ዚአነ ተጽሕፈ" - "የተጻፈው ሁሉ እኛ ልንማርበት: ልንገሠጽበት ነውና" (ሮሜ. 15:4) ልናስተውል ይገባናል::
††† ዜና ቅዱሳን የሚነገረን እንደ ታሪክ እንዲሁ ሰምተን እንድናልፈው አይደለም::
1.ከልቡ ለሚሰማው (ለሚያነበው) በረከት አለው::
2.ከቅዱሱ (ቅድስቷ) ቃል ኪዳን በእምነት ተካፋይ መሆን ይቻላል::
3.ቅዱሳኑ ክርስትናቸውን ያጸኑበት: የጠበቁበትና ለሰማያዊ ክብር የበቁበትን መንገድ እንማርበታለን:: ትልቁም ጥቅማችን ይሔው ነው::
ቁጥራችን ቀላል የማይባል የተዋሕዶ ልጆች ሕይወተ ቅዱሳንን እንደ ተራ ታሪክ ወይ ጀምረን እንተወዋለን:: ምናልባትም በግዴለሽነት እናነበዋለን:: ደስ ሲለንም ምስሉ ላይ 'like' የምትለውን ተጭነን እናልፈዋለን::
አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በደንብ አንብበን "ወይ መታደል!" ብለን አድንቀን እናልፋለን:: ማድነቃችንስ ጥሩ ነበር:: ግንኮ ቅዱሳኑ ለዚህ የበቁት የታደሉ ስለ ሆኑ ብቻ አይደለም:: ከእነርሱ የሚጠበቀውንም በሚገባ ሥለ ሠሩ እንጂ::
እግዚአብሔር የሚያዳላ አምላክ አይደለም:: "ኩኑ ቅዱሳነ እስመ ቅዱስ አነ-እኔ ቅዱስ እንደሆንኩ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ" (ዘሌ. 19:2, 1ጴጥ. 1:15) ብሎ የተናገረው ለጥቂት ወይም ለተለዩ ሰዎች አይደለም:: በስሙ ለሚያምኑ ሁሉ ነው እንጂ::
ስለሆነም እኛ ክርስቲያኖች: በተለይም ወጣቶች ከቀደምቶቻችን ተገቢውን ትምሕርት ወስደን ልንጸና: ልንበረታ: ለቤተ ክርስቲያናችንም "አለሁልሽ" ልንላት ይገባል:: ዛሬ እናት ቤተ ክርስቲያን በተለይ በከተሞች የወላድ መካን እየሆነች ነው::
"ይህን ያህል ሚሊየን ሰንበት ተማሪና ወጣት አላት" ይባላል:: ሲፈተሽ ግን በትክክለኛ ቦታው የሚገኘው ከመቶው ስንቱ እንደ ሆነ ለመናገርም ያሳፍራል:: የሆነውስ ሆነ: መፍትሔው ምንድነው ብንል:- እባካችሁ ከቅዱሳን ቀደምት ክርስቲያኖች መሥራት ያለብንን ቀስመን: ከዘመኑ ጋር አዋሕደን (ዘመኑን ዋጅተን) ራሳችንን: ቤተ ክርስቲያንንና ሃገራችንን እንደግፍ:: ካለንበት ያለማስተዋል አዘቅትም እንውጣ::
ለዚህም ቁርጥ ልቡና እንዲኖረን አምላካችን ይርዳን ብለን ወደ ቅዱሳኑ ዜና ሕይወት እንለፍ::
ቅዱሳን ቆዝሞስና ድምያኖስ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ በምድረ ሶርያ ተወልደው ያደጉ የዘመኑ ክርስቲያኖች ናቸው:: አባታቸው በልጅነታቸው በማረፉ 5 ወንድ ልጆችን የማሳደግ ሃላፊነት በእናታቸው ትክሻ ላይ ወደቀ:: እናታቸው ቅድስት ቴዎዳዳ ትባላለች::
እጅግ የምትገርም: ቡርክት እናት ናት:: አምስቱ ልጆቿ "ቆዝሞስ: ድምያኖስ: አንቲቆስ: አብራንዮስና ዮንዲኖስ" ይባላሉ:: በእርግጥ ለአንዲት እናት የመጀመሪያ ጭንቀቷ "ልጆቼ ምን ይብሉ" ነው:: ለቅድስት ቴዎዳዳ ዋናው ጉዳይ ይሔ አልነበረም::
ጌታችን እንዳስተማረን "ኢትበሉ ምንተ ንበልእ: ወምንተ ንሰቲ: ወምንተ ንትከደን - ምን እንበላለን: ምን እንጠጣለን: ምንስ እንለብሳለን ብላችሁ አትጠጨነቁ" ብሏልና ዘወትር የምትጨነቀው ስለ ልጆቿ ሰማያዊ ዜግነት ነበር:: (ማቴ. 6:31)
በዚህም ምክንያት አምስቱም ልጆቿን ዕለት ዕለት ወደ ቤተ እግዚአብሔር ትወስዳቸው: ከቅዱስ ቃሉ ታሰማቸው: መንፈሳዊ ሕይወትን ታለማምዳቸው ነበር:: አምላክ ከእኛ የሚፈልገው በጐ ፈቃዳችንንና በቅንነት የሆነች ትንሽ ጥረታችንን ነውና ቅድስት ቴዎዳዳ ተሳካላት:: ልጆቿ በአካልም: በመንፈሳዊ ሕይወትም አደጉላት::
ዘመኑ እንደ ዛሬ ተድላ ሥጋ የበዛበት ሳይሆን ክርስቲያን መሆን ለሞት የሚያበቃበት ነበር:: ከዚህ በፊት እንደ ተመለከትነው ከክርስቶስ ልደት 275 ዓመታት በኋላ በሶርያና በሮም የነገሡት ሁለቱ አራዊት (ዲዮቅልጢያኖስና መክስምያኖስ) ክርስቲያኖችን ከዋሉበት አላሳድሩ: ካደሩበትም አላውሉ አሉ::
ቀዳሚ ፈተናዋን በሚገባ የተወጣችው ቅድስት ቴዎዳዳ ይህኛውንም ትጋፈጠው ዘንድ አልፈራችም:: ግን ከልጆቿ ጋር መመካከር ነበረባትና ለውይይት ተቀመጡ:: ሦስቱ ልጆቿ ከልጅነታቸው ጀምረው ሲሹት የነበረውን ምናኔ መረጡ::
ቅድስቷ እናት በምርጫቸው መሠረት ቅዱሳን አንቲቆስ: ዮንዲኖስና አብራንዮስን መርቃ ወደ በርሃ ሸኘች:: እርሷም ከሁለቱ ቅዱሳን ልጆቿ ቆዝሞስና ድምያኖስ ጋር ቀረች::
እነዚህ ቅዱሳን በከተማ የቀሩት ግን ዓለም ናፍቃቸው አይደለም:: በእሥራት መከራን የሚቀበሉ የእግዚአብሔርን ቅዱሳን ያገለግሉ ዘንድ ነው እንጂ::
ቅድስት ቴዎዳዳ በቤቷ ነዳያንን ስትቀበልና ስታበላ ሁለቱ ቅዱሳን ልጆቿ ቀኑን ሙሉ እየዞሩ እሥረኞችን (ስለ ክርስቶስ የታሠሩትን) ሲጠይቁ: ሲያጽናኑ: ቁስላቸውን ሲያጥቡ አንጀታቸውንም በምግብ ሲደግፉ ይውሉ ነበር::
ይሕ መልካም ሥራቸው ለፈጣሪ ደስ ቢያሰኝም አውሬው ዲዮቅልጢያኖስን ግን ከመጠን በላይ አበሳጨው:: ወዲያውኑ ተይዘው እንዲቀርቡለት አዘዘ:: በትዕዛዙ መሠረትም ቆዝሞስና ድምያኖስ ታሥረው ቀረቡ::
"እንዴት ብትደፍሩ ትዕዛዜን ትሽራላችሁ! አሁንም ከስቃይ ሞትና ለእኔ ከመታዘዝ አንዱን ምረጡ" አላቸው:: ቅዱሳኑ ምርጫቸው ግልጽ ነበር:: ከክርስቶስ ፍቅር ከቶውኑ ሊለያቸው የሚችል ኃይል አልነበረምና:: (ሮሜ. 8:36)
ንጉሡም "ግረፏቸው" አለ:: ልብሳቸውን ገፈው: ዘቅዝቀው አሥረው: በብረትና በእንጨት ዘንግ ደበደቧቸው:: ደማቸውም መሬት ላይ ተንጠፈጠፈ:: እነርሱ ግን ፈጣሪን ይቀድሱት ነበር::
ይህ ዜና ፈጥኖ ወደ እናታቸው ደርሶ ነበርና ቅድስት ቴዎዳዳ እየባከነች ወደ ሰማዕታት አደባባይ ሮጠች:: አንዲት እናት ልጆቿ በአደባባይ ተሰቅለው ደማቸው ሲንጠፈጠፍ ስታይ ምን ሊሰማት እንደሚችል የሚያውቅ የደረሰበት ብቻ ነው::
ግን ክብራቸውን አስባ ተጽናናች:: ፈጥናም በሕዝቡ መካከል ስለ ሰነፍነቱ ከሀዲውን በድፍረት ዘለፈችው:: ንጉሡም በቁጣ አንገቷን በሰይፍ አስመታት:: ሁለቱ ቅዱሳን ይህንን በዓይናቸው አዩ:: አንዲት ነገርንም ተመኙ:: የእናታቸውን አካል የሚቀብር ሰው::
ግን ደግሞ ሁሉ ስለ ፈራ የቅድስቷ አካል መሬት ላይ ወድቆ ዋለ:: ያን ጊዜ ተዘቅዝቆ ሳለ ቅዱስ ቆዝሞስ አሰምቶ ጮኸ:: "ከእናንተ መካከል ለዚህች ሽማግሌ ጥቂት ርሕራሔ ያለው ሰው የለም?" ሲልም አዘነ:: ድንገት ግን ኃያሉ የጦር መሪ ቅዱስ ፊቅጦር ደረሰ::
ሰይፉን ታጥቆ: በመካከል ገብቶ የቅድስቷን አካል አነሳ:: በክብር ተሸክሞም ወስዶ ቀበራት:: በመጨረሸ ግን የሦስቱ ወንድሞቻቸው ዜና በመሰማቱ ከበርሃ በወታደሮች ተይዘው መጡ:: ከዚያም በብዙ መከራ አሰቃይተው በዚህች ቀን አምስቱንም አሰልፈው ገደሏቸው:: የክብር ክብርንም ከእናታቸው ጋር ወረሱ::
††† አምላከ ሰማዕታት ከትእግስታቸው: ከጽናታቸውና ከበረከታቸው ያሳትፈን::
Photo unavailableShow in Telegram
✝እንኳን አደረሰን!✝
☞በእንተ #እግዝእትነ #ማርያም ድንግል፤
ወበእንተ #ኢየሱስ #ክርስቶስ ወልዳ ፍቁር፤
☞ዝክሩ ስመ አበዊነ ቅዱሳን #ነቢያት #ሙሴ #ወአሮን #ዳዊት #ወሰሎሞን #ዕዝራ #ወዘካርያስ እለ አውኃዙ ተነብዮ በእንተ አማናዊት #እምነ #ጽዮን፡፡
"" ጸጋ ዘአብ ፥ ኂሩት ዘወልድ ሱታፌ ዘመንፈስ ቅዱስ እግዚአብሔር ፡ ወበረከታ ለእምነ #ጽዮን_ማርያም ፡ ተፋቅሮ #ዘነቢያት #ወዘሐዋርያት ወዘአበው ቀደምት ቅዱሳን ፡ ወትረ የኀሉ ምስሌየ ወምስለ ኩልክሙ፡፡ አሜን፡፡ ""
https://t.me/zikirekdusn
✝እንኳን አደረሰነ!
☞ወርኀ ኅዳር ቡሩክ። ወአመ ፳ወ፩፦
✝በዓል ዐቢይ ወክቡር ለዘመደ ክርስቲያን፥ በእንተ ቅድስት ጽዮን፥ ታቦተ ሕጉ ለእግዚአብሔር
✝ተዝካረ በዓላ፥ ለእግዝእትነ ቅድስት ድንግል በ፪ ማርያም፥ ወላዲተ አምላክ (ትምክህተ ዘመድነ፥ ወጸወንነ)
✝ቅድስት አኩስም፥ መካነ ነገሥት ጻድቃን (ወመካነ ጽዮን)
✝ጾመ ስብከተ ጌና፥ ዘነቢያት ወዘአበው ቀደምት ቅዱሳን (ወይእቲ ጾመ አዳም)
✝ወተዝካረ በዓሎሙ ለቅዱሳን፦ ምዕመነ ድንግል ወዓምደ ሥላሴ፥ አሮን ወመርትያኖስ፥ በጸሎተ ሚካኤል ድንግል፥ ወአበዊነ ጎርጎርዮሳት
❖ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦
✝ክቡራን ወዐቢያን ነቢያት፥ ሙሴ ወአሮን ካህናት (እለ ተልእክዋ ለጽዮን)
✝ክቡራን ወዐቢያን ነቢያት፥ ዳዊት ወሰሎሞን ነገሥት (እለ ተልእክዋ ለጽዮን)
✝ክቡራን ወዐቢያን ነቢያት፥ ዕዝራ ወዘካርያስ (እለ ተልእክዋ ለጽዮን)
✝ክቡራን ወዐቢያን፥ ነገሥት ጻድቃን፥ አብርሃ ወአጽብሐ (እለ ተልእክዋ ለጽዮን)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ አባ ጎርጎርዮስ ጻድቅ፥ ገባሬ መንክራት፡ ወሊቀ ጳጳሳት ዘእምብሔረ ሮሜ፥ ዘደረሰ ብዙኃ ድርሳናተ (ዘቂሣርያ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ዘኬዎስ ሐጺር፥ ሐዋርያሁ ለእግዚእነ (እም፸፪ቱ አርድእት)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ አባ ዮሐንስ ጻድቅ፥ ብእሲ መስተጋድል ወአረጋዊ (ዘሀገረ አስዩጥ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ አባ ቆዝሞስ ጻድቅ፥ ሊቀ ጳጳሳት ዘሀገረ እስክንድርያ (ዘአመንደብዎ ተንባላት)
✝ቅድስት ወቡርክት፥ ዲቦራ ጻድቅት፥ ዘሀገረ ድልበት (እንተ ትሰመይ ጫብሬ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ አባ ተወልደ መድኅን ጻድቅ (ኢትዮጵያዊ)
✝ቅዱሳን ሰማዕታት፥ እልፍዮስ፡ ወዘኬዎስ፡ ወሮማኖስ፡ ወዮሐንስ፡ ወቶማስ፡ ወፊቅጦር፡ ወይስሐቅ (ዘሀገረ እስሙናይን)
❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡
Repost from ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
Photo unavailableShow in Telegram
✝ቅዱስ ዘኬዎስ አጭሩ✝
¹-² ወደ ኢያሪኮም ገብቶ ያልፍ ነበር። እነሆም ዘኬዎስ የሚባል ሰው፥ እርሱም የቀራጮች አለቃ ነበረ፥ ባለ ጠጋም ነበረ።
³ ጌታ ኢየሱስንም የትኛው እንደ ሆነ ሊያይ ይፈልግ ነበር፤ ቁመቱም አጭር ነበረና ስለ ሕዝቡ ብዛት አቃተው።
⁴ በዚያችም መንገድ ያልፍ ዘንድ አለውና ያየው ዘንድ ወደ ፊት ሮጦ በአንድ ሾላ ላይ ወጣ።
⁵ ጌታ ኢየሱስም ወደዚያ ስፍራ በደረሰ ጊዜ፥ አሻቅቦ አየና፦ ዘኬዎስ ሆይ፥ ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛልና ፈጥነህ ውረድ አለው።
⁶ ፈጥኖም ወረደ በደስታም ተቀበለው።
⁷ ሁሉም አይተው፦ ከኃጢአተኛ ሰው ጋር ሊውል ገባ ብለው አንጐራጐሩ።
⁸ ዘኬዎስ ግን ቆሞ ጌታን፦ ጌታ ሆይ፥ ካለኝ ሁሉ እኵሌታውን ለድሆች እሰጣለሁ፤ ማንንም በሐሰት ከስሼ እንደ ሆንሁ አራት እጥፍ እመልሳለሁ አለው።
⁹ ጌታ ኢየሱስም፦ እርሱ ደግሞ የአብርሃም ልጅ ነውና ዛሬ ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል፤
¹⁰ የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአለና አለው። \ሉቃ፲፱÷፩\
<<ከቅዱስ ዘኬዎስ በረከት ያድለን።>>
Repost from ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
Photo unavailableShow in Telegram
++"++ አፄ #ፋሲል ያሰሩትና ለ300 ዓመታት ታቦተ ጽዮን የኖረችበት ቤተ ክርስቲያን (እዚያው #አክሱም) ++"++
"#ማርያም #ጽዮን ለእግዚአብሔር ታቦተ ሕጉ::
ያንጽሐኒ እምፍቅረ ወርቅ ለማየ ኪዳንኪ አይጉ::
እስመ ፍቅረ ንዋይ ተብሕለ ለሰይጣን ኤረጉ::" (መልክዐ ኪዳነ ምሕረት)
<< ክብሯ ይብዛልን >>
https://t.me/zikirekdusn
Repost from ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
✞✞✞Saint John of Assiut/Asyut✞✞✞
=>He was one of the righteous stars that rose in the 4th and 5th centuries. Because his age was advanced, he was a contemporary and companion to many saints. After subduing his body in strife, edifying the faithful of Assiut (Lycopolis) with his sermons, and performing many miracles, he departed on this day in the end of the 5th (some say 4th) century at the age of 125 years.
✞✞✞May the God of the Saints indwell in us the tang and love, the grace and blessing of the True Zion - the Virgin Mary. And may He not deprive us from the blessings of the Fathers.
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 21st of Hedar
1. Saint Mary of Zion
2. Saint Gregory Thaumaturgus (the Roman)
3. Saint John of Assiut/ Asyut/ Lycopolis
4. Saint Cosmas/Cosma the 54th Pope of Alexandria
5. Saint Deborah of Dalbat
6. Saint Zacchaeus the Short
✞✞✞ Monthly Feasts
1. The Gregories
2. Abune Memene Dingel
3. Abune Amde Selassie
4. Abba Aron/Aaron the Syrian
5. Abba Martinianus (Marcian) the Righteous
✞✞✞“For the nation and kingdom that will not serve thee shall perish; yea, those nations shall be utterly wasted . . . The sons also of them that afflicted thee shall come bending unto thee; and all they that despised thee shall bow themselves down at the soles of thy feet; and they shall call thee, The city of the Lord, The Zion of the Holy One of Israel.”✞✞✞
Isa. 60:12-14
✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞
(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
Repost from ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
7. And in the 4th century, the Righteous Emperors Abreha and Atsbeha built a beautiful church with 12 chapels for our Lady and on this day it was consecrated by the Lord.
8. In addition, time and again, when the church was demolished by Yodit Gudit (Judith) and Ahmed Gragn (Ahmad ibn Ibrahim al-Ghazi), the Ark of Zion was moved to Ziway. And when the church was rebuilt, its consecrations were held on Hedar 21 (November 30). For the above reasons and others, this feast is exceptional.
✞And we call the True Zion, the Mother of Light – the Virgin Mary as✞
=>Saint!
=>Though the epithet “Saint” is given to all holy women, its meaning becomes different when applied to the Virgin Mary. And that is because she is “Holy of holies, wholesome of the pure, blessed of the sacred and elect of the chosen.”
✞She is greater to all the children of men. Let alone the children of men, she is greater to the pure angels in wholesomeness and holiness. She is the Mother of Light, the Theotokos and the pride of our human nature.
✞And when we call our Lady “Holy - A Saint” we mean, “Preserved, immaculate, honored, and inimitable”.
1. Our Lady is called “Immaculate”. [That is because] when other people (saints) are said to be pure it is purity from evil deeds and speech, and not from sinful thoughts. However, our Lady is pure from the sins of speech, deed, and thought [which makes her immaculate]. As it says,
“To whom was it given, from the children of men, to keep from thinking sin (sinful thoughts). This was not even possible to the angels.”
(Introductory part of “The Miracles of Mary”)
2. We call her “Preserved” as well. [And that is because other] women are preserved in virginity temporarily but later on, they will lose that status. However, our Lady was a Virgin before conceiving [the Lord], during conception [of the Lord], after conception, before giving birth, while giving birth and after giving birth. [Hence she is preserved in perpetual virginity.]
And that is as the Saint had said, “Preserved in virginity and without corruption/sin.” (St. Yared/Jared)
In addition, it is as the Great St. Basil had said, “Mary, perpetually virgin.” (The Book of the Divine Liturgy – Anaphora of St. Basil, No. 73)
3. We also call the Virgin “Honored”. [And that is because] other women are given honor [not negating their labors] for the fact that they have bore saints, martyrs, prophets and apostles. However, we honor our Lady saying, “The Mother of God - Theotokos”.
4. We furthermore call our Lady “Inimitable”. And that is because no other woman was a mother while a virgin, a Lady while a servant and has brought forth milk while a virgin (a virgin’s milk) except her.
✞✞✞Saint Gregory of Rome - Thaumaturgus✞✞✞
=>He is one of the most renowned scholars of the Church and is known with his epithet “Thaumaturgus - Wonderworker”. And he was called Thaumaturgus for the great miracles he performed.
✞St. Gregory, who was born and raised in the Roman Empire in 4th century, before he became an ascetic, learned the Holy Scriptures. And while he was in the desert, because the Bishop of Rome (a Bishop in Rome) departed, the fathers held vigils wanting one whom they could appoint. Hence, God told them, “Find Gregory of the desert.”
✞Saying ”Alright” when they went to the desert to look for him, as he shuns vainglory, he hid from them. Grieved, they returned to the bishopric, placed the Gospel on the throne and went their ways. At that moment, a holy angel descended and instructed him, “O Gregory! You should go.”
✞Thus, he went to the city and while St. Gregory the Theologian (Gregory Nazianzus) was present (per the Ethiopian Tradition), he was consecrated. And after writing many works, keeping the flock of Christ and performing wondrous miracles, he departed on this day.✞And the following was one of the marvels that he performed.
✞At one time, when brothers had difficulty quarreling over a lake that they had inherited from their father, he dried the lake miraculously and reconciled them.
Repost from ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
#Feasts of #Hedar_21
✞✞✞On this day we commemorate Saint Mary of Zion (Mary the Abode of God) and the Saints Gregory Thaumaturgus and John of Assiut✞✞✞
✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞
✞✞✞Saint Mary of Zion✞✞✞
=>Zion means “a fortress, a refuge” and also has the meaning “The abode of God”. It (Zion) directly is a name used for the City of David – the hill and for the Ark of the Covenant. However, in its typological mystery it is used for the Virgin Mary, for the Church and for the Heavenly Kingdom.
✞God, after the age of the Patriarchs (Fathers), gave the Ark of Zion (the Ark of the Covenant) to Israel through St. Moses that it be their honor, splendor and fortress. (Exod. 31:18) And as it was with them for 500 years, it acted like a bridge amid them and God.
✞Thereafter, when the Proprietor willed, during Menelik I (Ibn Al-Melek/Ibn Al-Hakim – son of the wise) in the Era of Saba (Sheba), it came to Ethiopia. Hence, it is only a small number of years which are left for it to have stayed in our country for 3 thousand years. Consequently, per the Will of the Lord, having a portion of the Holy Cross and the Ark of Zion (the Ark of the Covenant) we live by His mercy.
✞Nonetheless, we know that there are many proselytizers that want to steal the Ark of Zion. But we are not vexed as it has come and is protected by the Will of God. Thus, we pray than be anxious. And we do not intreat basing rumors. And if its Proprietor Wills it, then no mighty man would stop its translocation.
✞”Tabote Tsion” - The Ark of Zion is most of the time known as “Tselate Kidan - the Tablets of the Covenant, Tabote Heg - the Ark of Law”. The Geez word “Tsele” means “Tablet” and “Tselate” is its plural form. And “Kidan” means “a covenant, an agreement” between God and the children of men.
✞In addition, the word “Tabot” means “an abode, an ark”. Hence, we call the tablets upon which the laws are written as “Tselat” whereas their ark as “Tabot”. And it is God Who brought forth “Tselat” (Tabot). And in the New Testament we find two places that mention about the Ark though they have a mystery and an exegesis behind them. (2 Cor. 6:16, Rev. 11:19)
✞Finally, we will see why we commemorate on Hedar 21 (November 30) St. Mary of Zion.
On this day,
1. We commemorate that the Ark of Zion (the Ark of the Covenant) was given to St. Moses the Arch-prophet. And we do this without forgetting that St. Moses had fasted for 40 days and 40 nights to obtain it.
2. The Ark of Zion was taken by the gentiles (Philistines) for the first time when Eli was the Archpriest. However, it demolished Dagon, the idol. (1 Sam. 5:1-)
3. During the reign of David, who was after God’s own heart, when the Ark came from the house of Obed–edom upon the cart of Abinadab, the Holy King in great jubilation sang before it and served. And to the extent of forgetting he was King, he sang for the Ark of God. And for that Michal despised him and she was made barren. (1Chr. 15:25) And our fathers, the scholars, have told us, “David has seen our Lady the Virgin Mary with prophecy [in the typology of the Ark].”
As it says,
“Mary, our mother, to you salutations
Whom we call our fortress
From afar seeing the beauty of your appearance
David while wearing a cloth of honor that was gleaming
Before the Ark of Law chanted and sang”
Arke of Hedar 21 (November 30) – Abba Arke Selus
4. During the reign of King Solomon (the lover of wisdom), when a wonderful Temple was built for the Ark and it entered, there was great joy. And God descended in a cloud and spoke with the King. (2Chr. 5:1, 1Kgs. 8:1)
5. And in that same era, by the Will of God, Emperor Menelik I (Ibn Al-Hakim) arrived in Ethiopia bringing with him the Ark of Zion.6. During the reign of Emperor Bazin (around 4 A.D) the True Zion, the Virgin Mary, arrived in Axum Zion in the time of her flight. And at that instant, when the 2 Zions (the Ark and the Virgin) met, great light engulfed the city, Axum.
Repost from ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
+እርሱም ወደ ከተማ ወርዶ ታላቁ ሊቅ ነባቤ መለኮት ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘእንዚናዙ ባለበት በዓለ ሲመቱ ተከብሯል:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ በዘመኑ ብዙ መጻሕፍትን ደርሶ: የክርስቶስን መንጋም ጠብቆ: ድንቅ ድንቅ ተአምራትንም ፈጽሞ በዚህች ቀን ዐርፏል:: ከተአምራቱም:-+ወንድማማቾች ከአባታቸው በወረሷት አንዲት ሐይቅ እየተጣሉ ሲያስቸግሩ በጸሎቱ ሐይቁን የብስ አድርጐ አስታርቁዋቸዋል::
+"+ ✝ቅዱስ ዮሐንስ ዘአስዩጥ✝ +"+
=>በ4ኛውና በ5ኛው መቶ ክ/ዘመናት ከተነሱ ከዋክብት ጻድቃን አንዱ ነው:: እድሜው በጣም ረዥም በመሆኑ የብዙ ቅዱሳን ባልንጀራም ነበር:: በገድል አካሉን ቀጥቅጦ: በስብከትም የአስዩጥን (አሲዩትን) ምዕመናን አንጾ: ብዙ ተአምራትንም ሠርቶ በተወለደ በ125 ዓመቱ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ በዚህች ቀን ዐርፏል::
=>አምላከ ቅዱሳን የአማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያምን ጣዕሟን ፍቅሯን: ጸጋ በረከቷን ያሳድርብን:: ከአበው በረከትም አይለየን::
=>ኅዳር 21 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅድስት ጽዮን ድንግል ማርያም
2.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘሮሜ
3.ቅዱስ ዮሐንስ ዘአስዩጥ
4.ቅዱስ ቆዝሞስ ሊቀ ዻዻሳት
5.ቅድስት ዲቦራ ዘድልበት
6.ቅዱስ ዘኬዎስ ሐጺር
=>ወርኀዊ በዓላት
1.አበው ጎርጎርዮሳት
2.አቡነ ምዕመነ ድንግል
3.አቡነ አምደ ሥላሴ
4.አባ አሮን ሶርያዊ
5.አባ መርትያኖስ ጻድቅ
=>++"++ ለአንቺም የማይገዛ ሕዝብና መንግስት ይጠፋል:: እነዚያ አሕዛብም ፈጽመው ይጠፋሉ . . . የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ:: የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ:: የእግዚአብሔርም ከተማ: የእሥራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል:: ++"++ (ኢሳ. 60:12)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
https://t.me/zikirekdusn
Repost from ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
✞✞✞✝ እንኩዋን ለጽዮን "ማርያም ማሕደረ አምላክ" እና ለቅዱሳኑ "ጐርጐርዮስ ወዮሐንስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
+*"+✝ ጽዮን ማርያም✝ +"*+
=>"ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው:: አንድም በምሥጢሩ "ማሕደረ አምላክ" ማለት ነው:: ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም: ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል::
+እግዚአብሔር ከዘመነ አበው በሁዋላ በጊዜው ለእሥራኤላውያን ክብር: ሞገስ: አምባ የምትሆናቸውን ታቦተ ጽዮንን በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት ሰጥቷቸዋል:: (ዘጸ. 31:18) ከዚያም ለ500 ዓመታት ከእነሱ ጋር በመሆኗ በፈጣሪና በእነሱ መካከል ድልድይ ሆና ኖራለች::
+ከዚያም ባለቤቱ ሲፈቅድ በዘመነ ሳባ: በቀዳማዊ ምኒልክ (እብነ መለክ-እብነ ሐኪም) አማካኝነት ወደ ኢትዮዽያ መጥታለች:: እነሆ በሃገራችን የ3ሺ ዓመት ቆይታዋን ልትደፍን የቀራት ጥቂት ዓመታት ብቻ ናቸው:: ጌታ እንደ ፈቀደ ቅዱስ መስቀሉንና ታቦተ ጽዮንን ይዘን ይሔው በቸርነቱ እንኖራለን::
+ያም ሆኖ ታቦተ ጽዮንን መስረቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀሳጢዎች እንዳሉ እናውቃለን:: ግን አንጨነቅም:: ምክንያቱም የመጣችውም: የምትጠበቀውም በፈቃደ እግዚአብሔር ነውና እንጸልያለን እንጂ አንጨነቅም:: በተለያየ ወሬም ራሳችንን አናማጥንም:: ባለቤቱ እንድትሔድ ከፈቀደ ደግሞ ማንም ጉልበተኛ አያስቀራትም::
+ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን: ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች:: "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው:: "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው::
+"ታቦት" ማለት "ማሕደር-ማደሪያ" እንደ ማለት ነው:: ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰላድው "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል:: ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው:: በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም 2 ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኛለን:: (2ቆሮ. 6:16, ራዕይ. 11:19)
+በመጨረሻም ኅዳር 21 ቀን ጽዮን ማርያምን የምናከብርባቸውን ምክንያቶች እንመለከታለን:: በዚህች ቀን:-
1.ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን) ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን:: ይሕ ሲሆንም ቅዱስ ሙሴ 40 መዓልት: 40 ሌሊት ጾሞ እንደ ተቀበለ ሳንዘነጋ ማለት ነው:: (ዘጸ. 31:18, ዘዳ. 9:19)
2.በዘመነ ኤሊ ሊቀ ካህናት ታቦተ ጽዮን በታሪኩዋ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ (ኢሎፍላውያን) እጅ ተማርካለች:: ግን ደግሞ ዳጐንን ቀጥቅጣዋለች:: (1ሳሙ. 5:1)
3.በዘመነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በአሚናዳብ ሠረገላ ሁና: ከአቢዳራ ቤት ስትመጣ ቅዱሱ ንጉሥ በታላቅ ሐሴት በፊቷ ዘመረ: አገለገለ:: ምድራዊ ክብሩን እስኪረሳ ድረስ ለታቦተ አምላክ ተቀኘላት:: በዚህም ሜልኮል ንቃው ማሕጸኗ ተዘግቷል:: (1ዜና. 15:25) ሊቃውንትም "ድንግል እመቤታችን ማርያም በትንቢት መነጽር ተመልክቷል" ብለውናል::
"ሰላም ለኪ ማርያም እምነ::
ዘሰመይናኪ ጸወነ::
ሶበ እምርሑቅ ርእየ ዘጽላሎትኪ ስነ::
ለቢሶ ዳዊት ልብሰ ክብር ዘየኀይድ ዓይነ::
ቅድመ ታቦተ ሕግ ኀለየ ወዓዲ ዘፈነ::" እንዲል:: (አርኬ ዘኅዳር 21)
4.በዘመነ ንጉሥ ሰሎሞን (መፍቀሬ ጥበብ) ግሩም የሆነ ቤተ መቅደስ ተሰርቶላት ስትገባ ታላቅ ሐሴት ተደርጉዋል:: እግዚአብሔርም በደመና ወርዶ ንጉሡን አነጋግሯል:: (2ዜና. 5:1, 1ነገ. 8:1)
5.በዚያው ዘመንም በፈጣሪ ፈቃድ ንጉሥ ምኒልክ ቀዳማዊ (ዕብነ ሐኪም) ታቦተ ጽዮንን ይዞ ወደ ኢትዮዽያ ገብቷል::
6.በዘመነ አፄ ባዜን (በ4 ዓ/ም አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ጽዮን በስደት መጥታ ገብታለች:: በዚህ ጊዜም 2ቱ ጽዮኖች ሲገናኙ ታላቅ ብርሃን አክሱምን ውጧታል::
7.በ4ኛው መቶ ክ/ዘመንም ነገሥት ጻድቃን አብርሐ ወአጽብሐ 12 መቅደሶች ያሏትን ግሩም ቤተ ክርስቲያን ለእመ ብርሃን ሠርተው በዚሁ ቀን በጌታችን ተቀድሷል::
8.በተጨማሪም በየጊዜው: ማለትም በዮዲት ጉዲትና በግራኝ አማካኝነት ስትፈርስ ወደ ዝዋይ ትሰደድ ነበር:: ተመልሳ ስትታነጽም ቅዳሴ ቤቷ የሚከበረው ኅዳር 21 ቀን ነው:: በእነዚህና በሌሎች ምክንያቶች ይህ በዓል ልዩ ነው::
+*" አማናዊት ጽዮን እመ ብርሃን ድንግል ማርያምን እንዲህ እንላታለን "*+
=>"ቅድስት" የሚለው ቃል ለሁሉም ቅዱሳት እናቶች ቢሰጥም ቅሉ ለድንግል ማርያም ሲሰጥ ግን ትርጉሙ ይለያል:: እርሷ "ቅድስተ ቅዱሳን: ንጽሕተ ንጹሐን: ቡርክት እምቡሩካን: ኅሪት እምኅሩያን" ናትና::
+ከሰው ልጆችም ሁሉ ትበልጣለች:: ይቅርና የሰው ልጅን ንጹሐን መላእክትንም በንጽሕናና በቅድስና ትበልጣቸዋለች:: እርሷ እመ ብርሃን: የአምላክ እናቱ: የሰውነታችን መመኪያ ናትና::
+እመቤታችንን "ቅድስት" ስንል "ጽንዕት: ንጽሕት: ክብርት: ልዩ" ማለታችን ነው::
1."ንጽሕት" ትባላለች:: ሌሎች ቅዱሳን ቢነጹ ከገቢር: ከነቢብ ኃጢአት ነው እንጂ ከኃልዮ ኃጢአት አይደለም:: እርሷ ግን ከነቢብ: ከገቢር: ከኃልዮ ንጽሕት ናት::
"ለመኑ ተውኅቦ ተደንግሎ ኅሊና: ለመላእክትሂ ኢተክህሎሙ-ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ከሰው ልጆች ለማን ተሰጠው: ይህስ ለመላእክትም አልተቻላቸውም" እንዲል:: (ተአምረ ማርያም)
2."ጽንዕት" እንላታለን:: ሴቶች ቢጸኑ ለጊዜው ነው እንጂ በሁዋላ በጊዜው ተፈትሆ አለባቸው:: እመቤታችን ግን ቅድመ ጸኒስ: ጊዜ ጸኒስ: ድኅረ ጸኒስ: ቅድመ ወሊድ: ጊዜ ወሊድ: ድኅረ ወሊድ ድንግል ናትና::
¤"ጽንዕት በድንግልና አልባቲ ሙስና" እንዳላት:: (ቅዱስ ያሬድ)
¤ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስም "ወትረ ድንግል ማርያም-ማርያም ዘለዓለማዊት ድንግል ናት" እንዳለ:: (መጽሐፈ ቅዳሴ)
3.ድንግልን "ክብርት" እንላታለን:: ሌሎች ሴቶች ቢከብሩ ጻድቃን ሰማዕታትን: ነቢያት ሐዋርያትን ወልደው ነው:: እመቤታችንን ግን የምናከብራት "ወላዲተ አምላክ-የአምላክ እናቱ" ብለን ነውና::
4.እመቤታችንን "ልዩ" እንላታለን:: ከእርሷ በቀር እናት ሁና ድንግል: እመቤት ሁና አገልጋይ የሆነች: በድንግልና ወልዳ ወተትን (ሐሊበ ድንግልናዌን) ያስገኘች ሌላ ሴት የለችምና::
+"+✝ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ዘሮም✝ +"+
=>በቤተ ክርስቲያን እጅግ ስመ ጥር ከሆኑት ሊቃውንት አንዱ ሲሆን ብዙ ጊዜ የሚታወቀው "ገባሬ መንክራት" በሚለው ስሙ ነው:: ገባሬ መንክራት የተባለውም እጅግ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን በመሥራቱ ነው::
+በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በሮም ግዛት ሥር ተወልዶ ያደገው ቅዱስ ጐርጐርዮስ ከመመነኑ በፊት ቅዱሳት መጻሕፍትን ተምሯል:: እርሱ በበርሃ እያለም ከሮም ዻዻሳት የአንዱ በማረፉ ተሿሚ ፍለጋ አበው ሱባኤ ገቡ:: እግዚአብሔርም "የበረሃውን ጐርጐርዮስን ፈልጉት" አላቸው::
+"እሺ!" ብለው ፍለጋ በርሃ ቢሔዱ ውዳሴ ከንቱን ይጠላልና ተሰወረባቸው:: እነርሱም እያዘኑ ተመልሰው በመንበረ ዽዽስናው ላይ ወንጌልን አኖሩና ተለያዩ:: በዚህ ጊዜ ቅዱስ መልአክ ወርዶ "ጐርጐርዮስ ሆይ! ልትሔድ ይገባሃል" አለው::
