2025 سال در اعداد

272 650
مشترکین
-5524 ساعت
+107 روز
+1 35830 روز
آرشیو پست ها
Photo unavailableShow in Telegram
25'
አንጎላ 1 - 0 ዙምባቡዌ
⚽️ ዳላ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤ 36🤔 4👍 2
ሞሮኮ የክቡር ይድነቃቸው ተሰማን ስታዲየም ልታድስ ነው !
ሞሮኮ በቀጣይ አራት ስታዲየሞችን ደረጃቸውን ከፍ አድርጋ ለመገንባት ማቀዷን በይፋ አስታውቃለች።
ሀገሪቱ ከምትገነባቸው ስታዲየሞች መካከል ሞሮኮ ካዛብላንካ የሚገኘው እና በክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ስም የተሰየመው “ Stade de Tessema “ ቀዳሚው ነው።
የክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ስታዲየም 20,000 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም እንዲኖረው እድሳት ተደርጎለት እንደ አዲስ እንደሚሰራ ይፋ ተደርጓል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤ 358👏 82😁 7🔥 5👍 3😢 2
Photo unavailableShow in Telegram
ሴሜንዮ አርሰናልን ይመርጥ ነበር !
መድፈኞቹ አንቶይን ሴሜንዮን ለማስፈረም ጥረት ቢያደርጉ የተጨዋቹ የመጀመሪያ ምርጫ ሊሆኑ ይችሉ እንደነበር ተገልጿል።
ተጨዋቹ የአርሰናል ደጋፊ ሆኑ ማደጉ ሲገለፅ ወደ ኤምሬትስ ስታዲየም ማቅናት መፈለጉም የሚጠበቅ ነበር ተብሏል።
አርሰናል ሀሳቡ ጥር ላይ ሳይሆን ክረምት ላይ ማስፈረም ቢሆንም ከተጨዋቹ ወኪሎች ጋር የተወሰነ ንግግር አድርገው ነበር።
በተጨዋቹ በኩል በጥር የዝውውር መስኮት አዲስ ክለብ የመቀላቀል ከፍተኛ ፍላጎት መኖሩ ተገልጿል።
ይህንንም ተከትሎ የተጨዋቹ መዳረሻ ማንችስተር ሲቲ ለመሆን ተቃርቧል።
❤ 291😁 139👎 28👏 15👍 12🤔 4🎉 2😱 1
Photo unavailableShow in Telegram
ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹን ጠርቷል !
ማንችስተር ዩናይትድ በውሰት አቅንቶ የነበረውን የመሐል ሜዳ ተሰላፊ ቶቢ ኮልየር ወደ ክለቡ እንዲመለስ መጥራቱ ተገልጿል።
ተጨዋቹ በውሰት ለሻምፒዮን ሺፑ ክለብ ዌስትብሮም በመጫወት ላይ እንደነበር ይታወቃል።
ተጨዋቹ በአሁኑ ሰዓት ለህክምና ወደ ማንችስተር ዩናይትድ ተመልሶ እየተከታተለ መሆኑ ተዘግቧል።
ቶቢ ኮልየር ህክምናውን ተከታትሎ ሲያገግም ወደ ዌስትብሮም እንደማይመለስ ተገልጿል።
ዩናይትድ በዝውውር መስኮቱ ይሳተፋል ?
ቀያዮቹ ሰይጣኖች በጥር የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት ተሳትፎ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸው ተገልጿል።
ይሁን እንጂ ማንችስተር ዩናይትድ በዝውውሩ የሚሳተፈው ለረጅም ጊዜ የሚፈልጋቸው ተጨዋቾች በገበያው ካሉ መሆኑ ተነግሯል።
በሌላ በኩል ክለቡ ለጆሽዋ ዚርኪዜ የቀረበለትን ጥያቄ ለመመልከት የአፍሪካ ዋንጫ እስከሚጠናቀቅ መጠበቅ እንደሚፈልግ ተዘግቧል።
ዘገባው የ ዘ አትሌቲክ ነው።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
❤ 199😁 57👍 11👏 4🤔 4👎 3
Photo unavailableShow in Telegram
ለደዋዮ ለየት ያለ የጥሪ ማሳመሪያ ሙዚቃ መጋበዝ እንደሚችሉ ሰምተዋል? አገልግሎቱን ለማግኘት አሁኑኑ ወደ *722# ይደውሉ!
#SafaricomEthiopia
#MPESASafaricom
#furtheraheadtogether
👎 16❤ 12😁 1
Photo unavailableShow in Telegram
NUR TECHNOLOGIES
አዳዲስ እና ዱባይ ዩዝድ የሆኑ ላፕቶፓች
☑️HP
☑️Lenovo
☑️Dell
☑️Microsoft Surface
☑️MacBook
☑️Gaming Laptops
☑️Iphone & Samsung Phones
☑️Tablets
በተመጣጣኝ ዋጋ ከሙሉ ዋስትና ጋር እናቀርባለን።
ለበለጠ መረጃ ከስር የሚገኘውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
Join Our Telegram Channel for more Information
📱📱📱📱📱📱📱📱📱📱
https://t.me/NurTechnologies
📞0911646359
አድራሻ - ቦሌ መድኃኒለም ሰላም ሲቲ ሞል ፊት ለፊት ለአሚር ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ
❤ 23
Photo unavailableShow in Telegram
ካፍ የግብፅ ብሔራዊ ቡድንን ቀጥቷል !
የአፍሪካ እግር ኳስ የበላይ ካፍ የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ላይ የ 5,000 ዶላር የገንዘብ ቅጣት መጣሉን አስታውቋል።
ካፍ ብሔራዊ ቡድኑን የቀጣው ከዚምባቡዌ ጨዋታ በኋላ ተጨዋቾቹ እና አሰልጣኞቹ ለሚዲያ አስተያየት ለመስጠት ፍቃደኛ ባለመሆናቸው መሆኑ ተነግሯል።
ብሔራዊ ቡድኑ ዛሬም ያሳየውን ባህሪ የሚደግም እና የሚዲያ ግዴታውን የማይወጣ ከሆነ ከባድ ቅጣት እንደሚጠብቀው ካፍ አስጠንቅቋል።
ግብፅ ዛሬ አመሻሽ 12:00 ሰዓት ከደቡብ አፍሪካ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች።
❤ 180😁 54👍 41👏 12👎 4🥰 3
Photo unavailableShow in Telegram
“ አፍሪካ ዋንጫ ከአውሮፓ ዋንጫ የበለጠ ከባድ ነው “
ሞሮኳዊው የቀድሞ ተጨዋች እስማኤል ቤልማሌም የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ጠንካራ መሆኑን በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።
የቀድሞ ተጨዋቹ ሲናገርም “ የአፍሪካ ዋንጫ ከአውሮፓ ዋንጫ የበለጠ በጣም አሰቸጋሪ ነው ፤ ባህሉ እና ድባቡም ለየት ያደርገዋል ” ሲል ገልጿል።
አያይዞም “ ሞሮኮ በአውሮፓ ዋንጫ የምትወዳደር ቢሆን ቢያንስ ሁለት ዋንጫ ታሸንፍ ነበር “ በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
😁 294❤ 225👏 48👍 19💯 4🤬 1
Photo unavailableShow in Telegram
“ አፍሪካ ዋንጫ ከአውሮፓ ዋንጫ ይከብዳል “
ሞሮኳዊው የቀድሞ ተጨዋች እስማኤል ቤልማሌም የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ጠንካራ መሆኑን በሰጠው አስተያየት ተናግሯል።
የቀድሞ ተጨዋቹ ሲናገርም “ የአፍሪካ ዋንጫ ከአውሮፓ ዋንጫ የበለጠ በጣም አሰቸጋሪ ነው ” ሲል ገልጿል።
አያይዞም “ ሞሮኮ በአውሮፓ ዋንጫ የምትወዳደር ቢሆን ቢያንስ ሁለት ዋንጫ ታሸንፍ ነበር “ በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
Photo unavailableShow in Telegram
“ ያለን ስብስብ ለአራት ውስጥ በቂ ነው “ አሞሪም
የማንችስተር ዩናይትዱ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ያላቸው ስብስብ አራት ውስጥ ለማጠናቀቅ በቂ ስለመሆኑ እርግጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።
“ አሁን ካለንበት የተሻለ የማድረግ አቅሙ እንዳለን መናገር እችላለሁ " ያሉት አሞሪም “ ቡድኑ እንዲሻሻል መርዳት የምችል ይመስለኛል ብለዋል።
“ ሁሉም ተጨዋቾች ዝግጁ ከሆኑ የተሻለ እንዲጫወቱ መርዳት እችላለሁ ወደፊትም የተሻለ መሆን እንደምንችል አስባለሁ። “ ሩበን አሞሪም
😁 405👍 189❤ 82👎 14🤔 5🤩 5
Photo unavailableShow in Telegram
ካማቪንጋ በአንጎላ ትምህርት ቤት ከፍቷል !
ፈረንሳዊው የሪያል ማድሪድ አማካይ ኤድዋርዶ ካማቪንጋ በአፍሪካዊቷ ሀገር አንጎላ ትምህርት ቤት መክፈቱን ይፋ አድርጓል።
የእረፍት ጊዜውን በትውልድ ሀገሩ እያሳለፈ የሚገኘው ካማቪንጋ በተጨማሪም ለታዳጊዎች የእግርኳስ አካዳሚ መክፈቱን ገልጿል።
“ ሀገሬን ለመርዳት ለታዳጊዎች ትምህርት ቤት እና አካዳሚ ለመክፈት መርጫለሁ በጣም ደስተኛ ነኝ ቤተሰቦቼም ኮርተዋል።" ሲል ካማቪንጋ ተናግሯል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
❤ 496👏 110👍 20😢 2🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
ተጠባቂ የዛሬ መርሐ ግብሮች !
9:00 አዳማ ከተማ ከ መቻል
9:30 አንጎላ ከ ዚምቧቡዌ
12:00 ግብፅ ከ ደቡብ አፍሪካ
2:30 ዛምቢያ ከ ኮሞሮስ
5:00 ሞሮኮ ከ ማሊ
5:00 ማንችስተር ዩናይትድ ከ ኒውካስትል ዩናይትድ
@tikvahethsport @kidusyoftahe
❤ 189👍 30🔥 4👏 4😁 2
Photo unavailableShow in Telegram
“ ህልም እንዳይሳካ የሚያደርገው ውድቀትን መፍራት ነው “
የሞርኮ ብሔራዊ ቡድን በተጨዋቾቹ ልምምድ ስፍራ በትልቅ ስክሪን ለቡድኑ አነቃቂ መልዕክት አስመልክቶ ታይቷል።
በስፍራው በሚገኘው ስክሪን የሰፈረው አነቃቂ መልዕክት “ ህልም እንዳይሳካ የሚያደርገው ብቸኛ ነገር ውድቀትን መፍራት ነው “ ሲል ይነበባል።
አነቃቂ የፅሁፍ መልዕክቱ በአምስት አይነት ቋንቋዎች ለብሔራዊ ቡድኑ እይታ ቀርቧል።
የአፍሪካ ዋንጫው ቅድመ ግምት ያገኙት የአትላስ አንበሶቹ ከ 4️⃣9️⃣ አመታት በኋላ የውድድሩ ባለክብር ለመሆን ይፋለማሉ።
❤ 352🔥 45👍 29👏 17😁 7🙏 5👎 4
Photo unavailableShow in Telegram
“ የእኔ ከባዱ ተጋጣሚ ሜሲም ሮናልዶም አልነበሩም “ አሌሳንድሮ ፍሎሬንዚ
የቀድሞ ጣልያናዊ ተጨዋች አሌሳንድሮ ፍሎሬንዚ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ሊዮኔል ሜሲ ለእሱ አስቸጋሪ እንዳልነበሩ ተናግሯል።
“ ከሜሲ እና ሮናልዶ ጋር ተጫውቻለሁ ለእነሱ አክብሮት አለኝ ነገርግን ለእኔ ከባዱ ተጋጣሚ አልነበሩም “ ሲል ተደምጧል።
“ እኔን ያሰቃየኝ ተጨዋች ኢቫን ፔርሲች ነው “ የሚለው አሌሳንድሮ ፍሎሬንዚ “ እሱ በግራ ሆነ በቀኝ ምንም ለውጥ የለውም መሮጡን አያቆምም ከባድ ነበር “ ብሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
😁 472❤ 119👍 55🙏 3🥰 2
Photo unavailableShow in Telegram
“ ሁሉንም ዋንጫ🏆 የማሸነፍ አቅም አለን “ ዊሊያም ሳሊባ
የመድፈኞቹ የኋላ መስመር ተሰላፊ ዊሊያም ሳሊባ አርሰናል ዋንጫ ለማሸነፍ “ ጫፍ ላይ ነው “ ሲል ተናግሯል።
ቡድኑ በጥሩ ቁመና ላይ መሆኑን ያነሳው ሳሊባ “ በሁሉም ውድድሮች ላይ እየተፎካከርን ነው በዚሁ መቀጠል አለብን “ ብሏል።
አክሎም “ ሁሉንም የምንሳተፍባቸውን ውድድሮች የማሸነፍ አቅሙ እንዳለን እናውቃለን “ ሲል ካለፈው አመት መማር እንደሚገባ አሳስቧል።
“ ይህንን ሜዳ ላይ ማሳየት እና ዋንጫ ማሸነፍ መጀመር አለብን “ ሲል ጨምሮ ተናግሯል።
“ ትኩረት ማድረግ ፣ በራሳችን ማመን እና ተግተን መስራት ይኖርብናል ምክንያቱም በጣም አስፈላጊው ነገር በመጨረሻ ዋንጫ ማሸነፍ ነው።“ ዊሊያም ሳሊባ
❤ 647😁 517💯 34👎 15🔥 9👍 8🙏 8🥰 2👏 2
Photo unavailableShow in Telegram
ኪሊያን ምባፔ ሞርኮ መግባቱ ተነግሯል !
ፈረንሳዊው የሪያል ማድሪድ የፊት መስመር ተሰላፊ ኪሊያን ምባፔ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ሞሮኮ መግባቱ ተገልጿል።
ኪሊያን ምባፔ በነገው ዕለት የሞሮኮ እና ማሊን ጨዋታ ለመታደም በማሰብ ከቤተሰቡ ጋር ወደ ሞሮኮ ማቅናቱ ተነግሯል።
ምባፔ በጨዋታው እንዲገኝ ከቅርብ ጓደኛው አሽራፍ ሀኪሚ እና ከሞሮኮ ግብዣ እንደቀረበለት መዘገቡ ይታወሳል።
በተጨማሪም የፒኤስጂው ተጨዋች ኡስማን ዴምቤሌ በጨዋታው ሊገኝ እንደሚችል ተነግሯል።
ኡሴማን ዴምቤሌ በነገው ዕለት ወደ ሞሮኮ ሊያቀና እንደሚችል የፈረንሳይ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤ 452👍 61🔥 24👏 8💯 3🙏 1
Photo unavailableShow in Telegram
#EthPL
በ ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ1 አጠናቀዋል።
የፈረሰኞቹን ግብ ሀብታሙ ጉልላት ሲያስቆጥር ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ናትናኤል ዳንኤል ከመረብ አሳርፏል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
6️⃣ ቅዱስ ጊዮርጊስ :- 17 ነጥብ
1️⃣3️⃣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ :- 12 ነጥብ
ቀጣይ መርሐግብር ?
ሰኞ - መቐለ 70 እንደርታ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
እሮብ - ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ኢትዮጵያ መድን
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
❤ 74😁 11👍 9👎 3🤬 3
Photo unavailableShow in Telegram
ማድሪድ ከሳንቲያጎ በርናቦ ስንት ያገኛል ?
ሪያል ማድሪድ በዘንድሮው የውድድር ዘመን ከሳንቲያጎ በርናቦ ስታዲየም ከፍተኛ ገቢ እንደሚጠብቅ ተገልጿል።
ሎስ ብላንኮዎቹ ከስታዲየሙ ብቻ 400 ሚልዮን ዩሮ ገቢ ያገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል።
ገቢው የሚገኘው ከሙዚቃ ድግስ ፣ ከጉብኝት ፣ ከተለያዩ ዝግጅቶች እና ሬስቶራንት መሆኑ ተዘግቧል ።
ክለቡ ከስታዲየሙ የሚያገኘው ገቢ በ 31% ከፍ እንደሚል ሲገለፅ ሪከርድ ሆኖ ይመዘገባል ተብሎ ይጠበቃል።
❤ 175👍 32👎 12🔥 11
