Ethio telecom
Открыть в Telegram
We Simplify lives & accelerate Ethiopia’s digital transformation & beyond via delivering reliable communications, innovative digital solutions & seamless financial services that empower communities, businesses & nations. https://t.me/EthiotelecomChatBot
Больше2025 год в цифрах

306 706
Подписчики
-6324 часа
-347 дней
-1 24430 день
Архив постов
Фото недоступноПоказать в Telegram
በተራዘመ ክፍያ ሳምሰንግ ጋላክሲ A16 5G ስማርት ስልክ የግልዎ ያድርጉ!
🗓🤝 በወር 2,930 ብር (ለ12 ወራት) ወይም 5,426 ብር (ለ6 ወራት) ክፍያ ዘመናዊ ስማርት ስልክ የግልዎ ያድርጉ።
💁♂️ በ *127# ወይም በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_SuperApp “ቴሌ ዲቫይስ ፋይናንሲንግ” ሚኒ አፕ ተመዝግበው ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከሎቻችን ጎራ ይበሉ!
👉ማሳሰቢያ: የዕድሉ ተጠቃሚ ለመሆን ብድር ካለብዎ መክፈልዎን አይዘንጉ!
ኢትዮ ቴሌኮም ከአዋሽ ባንክ ጋር በአጋርነት
#Ethiotelecom #AwashBank #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
❤ 39👍 39😡 11
Фото недоступноПоказать в Telegram
አዲስ ነገር ይዘው የመጡት #ዘኔክሰስ የሞባይል ስልኮች!
🔆 ለተጠቃሚዎች ምቹ የሆኑ
🔋 ረጅም የባትሪ ዕድሜ ያላቸው
🗂 በ teleStorage አማካኝነት የራሳቸው የፋይል ማከማቻ ያላቸው
🤖 ቴሌብርን ጨምሮ ወሳኝ አፕሊኬሽኖች የተጫኑባቸው
🛜 ዋይፋይና ሆትስፖት ማስጠቀም የሚችሉ
ከ2 ጊ.ባ የሦስት ወራት ነጻ የዳታ ስጦታ ጋር እጅግ በተመጣጣኝ ዋጋ ቀርበዋል፤ ፈጥነው የግልዎ ያድርጓቸው።
📍በሁሉም የአገልግሎት ማዕከሎቻችን ያገኟቸዋል!
#znexus
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
❤ 32👍 18😁 6😢 1🤩 1
01:29
Видео недоступноПоказать в Telegram
ለብሮድባንድ ኢንተርኔት አገልግሎት እንዴት በቀላሉ በአርዲ ቻትቦት መመዝገብ ይቻላል?
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
31.06 MB
👍 31❤ 22👌 2
የላቀ ፍጥነት ከደጃፍዎ ደርሷል!
ኢትዮ ቴሌኮም የላቀ ፍጥነት ያለውን 4G ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ አገልግሎት በምዕራብ ሪጅን በነቀምት፣ ባኮ፣ ሻምቡ፣ ነጆ፣ ደምቢ ዶሎ እንዲሁም ጊምቢ ከተሞች ነባር ኔትወርኩን በማሳደግና አዳዲስ ግንባታ በማከናወን ከደጃፍዎ ማድረሱን በደስታ ይገልጻል!
የኢትዮ ቴሌኮም 4ጂ ኤል.ቲ.ኢ የላቀ ፍጥነት
የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት አጠቃቀም በእጅጉ ያሻሻላል፤ አገልግሎት አሰጣጥ፣ ምርታማነት እና ቢዝነስ ይቀለጥፋል፤ አኗኗር ይዘምናል!
የላቀ ፍጥነትን በተቀላቀሉት ነቀምት፣ ባኮ፣ ሻምቡ፣ አኖ፣ ሲሬ፣ ጉቴ፣ አርጆ፣ ነጆ፣ ደምቢ ዶሎ እንዲሁም ጊምቢ ከተሞች የነበረን ደማቅ ቆይታ ይህን ይመስላል።
በ4G የላቀ ፍጥነት
የፍጥነቱን ዓለም ይቀላቀሉ!
#ዲጂታል_ኢትዮጵያን_ዕውን_በማድረግ_ላይ
#4GLTE
#Ethiotelecom #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
❤ 37👍 22👌 4😡 4
የኢትዮ ቴሌኮም ማኔጅመንት አባላት እና ሠራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን አከበሩ!
ኩባንያችን “ትውልድን በሥነ-ምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!” በሚል መሪ ሀሳብ ለ22ኛ ጊዜ በትናንትናው ዕለት የተከበረውን ዓለም አቀፍ የፀረ- ሙስና ቀንን የኩባንያችን ማኔጅመንት አባላት፣ ሠራተኞች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ መርሃግብሮች አክብሯል።
በዓሉን አስመልክቶ የኩባንያችን የሰው ኃይል ቺፍ ኦፊሰር ጥላሁን ነጋሽ በመክፈቻ ንግግራቸው፤ ኩባንያችን እንደ አንድ የአገልግሎት ሰጪ ተቋም አመራሩና ሰራተኛው በሥነ-ምግባር በመታነጽ፣ የአገልጋይነት ባሕሪይን በመላበስ፣ በዲጂታል አገልግሎት የታገዘ አሰራርን በመተግበር፣ በግልጽነት እና በተጠያቂነት ስሜት ኃላፊነትን በመወጣት፣ ብልሹ አሠራርን በመከላከል ለደንበኞች ቀልጣፋና የላቀ አገልግሎት መስጠት የዜጎችን ሕይወት ማቅለል እና የኢትዮጵያን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠን እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎችን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አጽንኦት ተሰጥተውበታል፡፡
በዕለቱ ከፌደራል ስነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በዓሉን አስመልክቶ በድምፅ ተዘጋጅቶ የተላከ ሰነድን በማድመጥ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ የሃብት ምዝገባ ርክክብ ስነ-ስርዓት እና በኮሚሽኑ የተዘጋጀውን የጋራ የትብብር ሰነድ የፊርማ ሥነ-ሥርአት ተከናውኗል፡፡
በመጨረሻም በኩባንያችን የለማው አዲስ የሥነ-ምግባር መከታተያ እና የጥቆማ መቀበያ የጥሪ ማእከል (9488)፣ የኮሚሽኑ የጥቆማ መቀበያ (NCRS)፣ EIH የለማው የጥቆማ መቀበያ ሲስተሞችን የማስተዋወቅ ሥራዎች በመስራት እንዲሁም የጋራ የአቋም መግለጫ በማውጣትና ቃል በመግባት ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡
የኢትዮ ቴሌኮም ማኔጅመንት አባላት እና ሠራተኞች ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን አከበሩ!
ኩባንያችን “ትውልድን በሥነ-ምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!” በሚል መሪ ሀሳብ ለ22ኛ ጊዜ በትናንትናው ዕለት የተከበረውን ዓለም አቀፍ የፀረ- ሙስና ቀንን የኩባንያችን ማኔጅመንት አባላት፣ ሠራተኞች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተለያዩ መርሃግብሮች አክብሯል።
በዓሉን አስመልክቶ የኩባንያችን የሰው ኃይል ቺፍ ኦፊሰር ጥላሁን ነጋሽ በመክፈቻ ንግግራቸው፤ ኩባንያችን እንደ አንድ የአገልግሎት ሰጪ ተቋም አመራሩና ሰራተኛው በሥነ-ምግባር በመታነጽ፣ የአገልጋይነት ባሕሪይን በመላበስ፣ በዲጂታል አገልግሎት የታገዘ አሰራርን በመተግበር፣ በግልጽነት እና በተጠያቂነት ስሜት ኃላፊነትን በመወጣት፣ ብልሹ አሠራርን በመከላከል ለደንበኞች ቀልጣፋና የላቀ አገልግሎት መስጠት የዜጎችን ሕይወት ማቅለል እና የኢትዮጵያን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠን እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎችን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አጽንኦት ተሰጥተውበታል፡፡
በዕለቱ ከፌደራል ስነምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በዓሉን አስመልክቶ በድምፅ ተዘጋጅቶ የተላከ ሰነድን በማድመጥ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ የሃብት ምዝገባ ርክክብ ስነ-ስርዓት እና በኮሚሽኑ የተዘጋጀውን የጋራ የትብብር ሰነድ የፊርማ ሥነ-ሥርአት ተከናውኗል፡፡
በመጨረሻም በኩባንያችን የለማው አዲስ የሥነ-ምግባር መከታተያ እና የጥቆማ መቀበያ የጥሪ ማእከል (9488)፣ የኮሚሽኑ የጥቆማ መቀበያ (NCRS)፣ EIH የለማው የጥቆማ መቀበያ ሲስተሞችን የማስተዋወቅ ሥራዎች በመስራት እንዲሁም የጋራ የአቋም መግለጫ በማውጣትና ቃል በመግባት ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡
👍 4❤ 3
Фото недоступноПоказать в Telegram
ቀልጣፋ ብድር በቴሌብር!
ቴሌብር ከአዋሽ ባንክ ጋር በመተባበር ባቀረበው ጥላ የፋይናንስ አገልግሎት ተጠቅመን፤ በ75 ቀናት ተመላሽ የሚደረግ እስከ 16 ሺህ ብር አነስተኛ ብድር፤ በቴሌብር ደሞዝ ለሚቀበሉ የቀረበ እስከ 5 ወራት ደሞዝ በ16 ወራት ተመላሽ የሚደረግ ብድር እንዲሁም የጥላ አነስተኛ ቁጠባ አገልግሎት ተጠቃሚ እንሁን!
#ስንበደር_እንዲህ_ነን
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን
#ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን
#ስንጭን_እንዲህ_ነን
#ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
👍 45❤ 33😡 6🤝 4🙏 3
Фото недоступноПоказать в Telegram
ቀልጣፋ ብድር በቴሌብር!
ቴሌብር ከአዋሽ ባንክ ጋር በመተባበር ባቀረበው ጥላ የፋይናንስ አገልግሎት ተጠቅመን፤ በ75 ቀናት ተመላሽ የሚደረግ እስከ 16 ሺህ ብር አነስተኛ ብድር፤ በቴሌብር ደሞዝ ለሚቀበሉ የቀረበ እስከ 5 ወራት ደሞዝ በ16 ወራት ተመላሽ የሚደረግ ብድር እንዲሁም የጥላ አነስተኛ ቁጠባ አገልግሎት ተጠቃሚ እንሁን!
የኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ የሥራ አመራሮች በካምቴል (CAMTEL) ስትራቴጂያዊ ጉብኝት አከናወኑ
ዋና ስራ አስፈጻሚያችን ፍሬህይወት ታምሩ እና የካምቴል ዋና ስራ አስኪያጅ ጁዲት ያህ ሰንደይ የመሩት የልዑካን ቡድን፤ በካሜሩን የነበረውን ስኬታማ የትብብር ሳምንት በካምቴል የቴክኒክ ተቋማት ላይ ባደረገው ጉብኝት አጠናቋል።
ይህ የጋራ ጉብኝት በሁለቱ ተቋማት መካከል የተፈጠረውን ጥምረት ወደ ተግባር ለማሸጋገር እና ስትራቴጂያዊ እቅዶችን ለመተግበር ወሳኝ ምዕራፍ ከፋች ሆኖ አልፏል። ጉብኝቱ አዲሱን የትብብር ስምምነት ከመግባት ባለፈ፣ በፍጥነት ወደ ልምድ እና የቴክኒክ እውቀት ልውውጥ የተሸጋገረበት መድረክም ነበር።
የተቋማችን አመራሮች የካምቴልን የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት የጎበኙ ሲሆን፤ የኔትወርክ ኦፕሬሽን ማዕከልን (Network Operations Center)፣ የዲጂታል ደንበኞች አገልግሎት የሚሰጥበትን ብሉ ስቶር ዋርዳን (Blue Store Warda) እና የዛሜንጎ ዳታ ሴንተርን (Zamengoe Data Center) ተመልክተዋል።
በቆይታቸውም የካምቴል የሥራ ኃላፊዎች ዝርዝር ገለጻ ለኩባንያችን አመራሮች አቅርበዋል። ጉብኝቱን ተከትሎ በሁለቱ ተቋማት አመራሮች መካከል በተደረገ ውጤታማ ውይይት፣ በቀጣይ በሚወሰዱ አፋጣኝ የትብብር እርምጃዎች ላይ የጋራ መግባባት ተፈጥሯል።
የጥምረቱን ራዕይ ለብዙሃን መገናኛዎች ያብራሩት የኩባንያችን ዋና ስራ አስፈጻሚያችን፤ ይህ አጋርነት ከተለመደው የቢዝነስ ስምምነት በላይ መሆኑንና "ዲጂታል ካሜሩንን" እውን ለማድረግ የተቀመጠ የጋራ ቁርጠኝነት መሆኑንም ጭምር አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።
#Ethiotelecom #Camtel #GSMA #ITU #G6Countries
❤ 56👍 18👏 8🥰 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
✨🎁 አየር ሰአትና ጥቅል ከውጭ አገራት ይቀበሉ፤ 15% ተጨማሪ ቦነስ ያግኙ!!
ከውጭ ሀገራት በአጋሮቻችን
✅ Ethio remit ✅ EZECALL
✅ Prepaynation ✅ ding
✅ reloady ✅ Omnivas
✅ Boss
በኩል ከ200 ብር ጀምሮ የተላከልዎን የሞባይል አየርሰዓት ወይም ጥቅል ሲቀበሉ:-
💁♂️ ለ15 ቀናት የሚያገለግል የ15% ተጨማሪ ስጦታ እናበረክትልዎታለን፡፡
ደንብና ሁኔታዎች 👉 https://bit.ly/4j7iOcI
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
❤ 35👍 12🙏 3🎉 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
እንኳን ለ20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!
ኅዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
👍 38❤ 26🙏 6🤪 6
ከካምቴል ጋር ስትራቴጂካዊ የትብብር ስምምነት ይፋ ለማድረግ በካሜሩን በነበረን ቆይታ፤ ከመደበኛው መርሃ ግብራችን ባሻገር ለየት ያለ ጊዜ አሳልፈናል።
ከአፍሪካ ቀደምት የዓለም አቀፍ የእግርኳስ ኮከቦች አንዱ ከሆነውና ድንቅ ብቃቱ ትውልድን ካነቃቃው፣ እንዲሁም ለአህጉራችን ኩራት ከሆነው ከታዋቂው የካሜሩን የእግር ኳስ ፈርጥ ሮጀር ሚላ ጋር በመገናኘታችን ደስ ብሎናል፡፡
ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እና የልዑካን ቡድኑ አባላት፤ ይህንን አንጋፋ የእግር ኳስ ኮከብ በአካል በማግኘት ለስፖርቱ ዓለም ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድናቆታችንን ገልጸናል።
ይህ ከሮጀር ሚላ ጋር የነበረን አስደሳች ቆይታ ለጉብኝታችን ልዩ ትዝታ እና ድምቀት ሰጥቶታል። በህዝቦቻችን መካከል ያለውን ጥብቅ ትስስር፣ ባህል እና ሀገሮቻችንን የሚያስተሳስረውን የላቀ የስፖርት ስሜት እንድናስታውስ አድርጎናል።
በካሜሩን መንግሥት፣ በካምቴል እና በካሜሩን ህዝብ ለተደረገልን ልዩ መስተንግዶ እና ሞቅ ያለ አቀባበል ከልብ እናመሰግናለን!
በአጋርነት፣ በዓላማ እና በምርጥ ተሞክሮ የተሞላ የማይረሳ ጉዞ!
#Ethiotelecom #CAMTEL #RogerMilla #Cameroon #Ethiopia
❤ 46👍 41
Фото недоступноПоказать в Telegram
መልካም የእረፍት ቀን!
#Sunday
#StayConnected
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
👍 39❤ 28🥰 5🥴 4🙏 3🤩 2🤗 1
Cameroon's Prime Minister Hails Strategic Alliance Between Ethio telecom and CAMTEL.
The Prime Minister of Cameroon, His Excellency Chief Dr. Joseph Dion Ngute, received the CEO of Ethio telecom, Frehiwot Tamru, and the Director General of CAMTEL, Judith Yah Sunday.
During the session, the Prime Minister emphasized that digitalization is the cornerstone of sustainable economic growth, a goal best achieved through the robust collaboration of African operators. Appreciating the initiative taken by both institutions, His Excellency pledged his government's unwavering support for this strategic alliance to ensure the digital transformation happen in Ethiopia to be replicated in Cameroon .
Ethio telecom CEO Frehiwot Tamru presented Ethiopia’s remarkable digital transformation journey, highlighting the decisive role played by Ethio telecom in expanding nationwide connectivity, ensuring affordability, and accelerating financial inclusion.
Read More
❤ 65👍 25👏 3
ኢትዮ ቴሌኮም እና ካምቴል በካሜሩን የዲጂታል ሽግግርን ለማፋጠን የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ተፈራረሙ!
ኢትዮ ቴሌኮም ከካምቴል (CAMTEL) ጋር የካሜሩንን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠን የሚያስችል ታሪካዊ የማስተር ሰርቪስ የኮንትራት ስምምነት በካሜሩን ያውንዴ ከተማ ተፈራርሟል!
ይህ ስምምነት፤ የካምቴል የስራ ሃላፊዎች ወደ ሀገራችን በመምጣት ኩባንያችን በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ" ግንባታ ውስጥ ያሳየውን የላቀ የቴክኖሎጂ አመራር ከተመለከቱ በኋላ፣ ተሞክሮውን ወደ ካሜሩን ለመውሰድ ከነበራቸው ፍላጎት የመነጨ ነው።
በዚህም መሰረት ሁለቱ ኦፕሬተሮች በካሜሩን የፋይናንስ ተደራሽነትን የሚያረጋግጥ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ለማስፋፋት፣ ብሄራዊ ክላውድ በመገንባት የመንግስት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ለማድረግ፣ የሞባይል ኔትወርክ ጥራትን ለማረጋገጥ እንዲሁም የካምቴልን አሰራር በይበልጥ በማዘመን ደንበኛ ተኮር ባህል ለመገንባት በጋራ ይሰራሉ።
በተጨማሪም ስምምነቱ፤ ለካሜሩን የዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሆኑ ተቋማትና ቢዝነሶች የሚያቀላጥፉ ዲጂታል መፍትሄዎችን፣ የተጨማሪ እሴት እና የኢንተርኮኔክት አገልግሎቶችን በጋራ ለመተግበር ያስችላል፡፡
ይህ ስምምነት በኩባንያችን የ‘ቀጣዩ አድማስ፡ ዲጂታልና ከዚያም ባሻገር 2028 ስትራቴጂ’ መሰረት፣ ድንበር ተሻጋሪ አገልግሎት በማቅረብና አህጉራዊ ትብብርን በማጎልበት የዲጂታል አፍሪካን ጉዞ ለማፋጠን የሚያስችል ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
#Ethiotelecom #Camtel #DigitalAfrica #DigitalCameroon
❤ 54👍 37🤣 6😡 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
ፓርኪንግ ዘምኗል!
ደህንነታቸው በተጠበቀው በዘመናዊዎቹ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የመኪና ማቆሚያ መኪናዎን ያለሃሳብ አቁመው፤ ክፍያዎን ደግሞ በቴሌብር ሱፐር አፕ መክፈል ይችላሉ!
ቴሌብርን በስልካችን በዚህ ሊንክ
https://bit.ly/telebirr_SuperApp ጭነን ስንመዘገብ እንዲህ ነን!
#ስንከፍል_እንዲህ_ነን
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን
#ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን
#ስንጭን_እንዲህ_ነን
#ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
👍 23❤ 21🤔 4🤩 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
✨🎶 ያልተገደበ ምርጥ ምርጥ ሙዚቃዎችን ለመስማት ዝግጁ ነዎት?
የዲጂታል ሕይወት እሴትን የሚጨምሩ፤ የሚወዷቸውን ዜማዎች ያለገደብ የሚያደምጡበት፤ ልዩ ጥቅማ ጥቅሞችን እና የዳታ አጠቃቀምን ባገናዘበ መልኩ ሁሉንም በአንድ አጣምሮ Boomplay አቅርቧል።
📩 ለዕለታዊ፣ ለሳምንታዊ ወይም ለወርኃዊ ጥቅሎች A፣ B ወይም Cን ወደ 8894 ይላኩ።
📲 በመተግበሪያ Boomplayን ያውርዱ → ወደ ፕሮፋይል ይሂዱ → በስልክ ቁጥርዎ እና በፒን አማካኝነት ይግቡ!
🛑 አገልግሎቱን ለማቋረጥ Stop A፣ Stop B ወይም Stop Cን ወደ 8894 ይላኩ።
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
❤ 35👍 19🥰 3😡 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
✨📊 በቢዝነስ ኤክሴል የንግድ ሥራዎን ያዘምኑ፤ በየሳምንቱ 50,000 ብር ተሸላሚ ይሁኑ!
ጠቃሚ የንግድ መረጃዎች እና ቴምፕሌቶችን በአንድ ቦታ በሚያገኙበት ቢዝነስ ኤክሴል ተጠቅመው የንግድ ስራዎን ያዘምኑ፤ በሳምንታዊ ጥያቄና መልስ ውድድር በመሳተፍ በየሳምንቱ 50,000 ብር ያሸንፉ።
✅ ለመመዝገብ ok ብለው ወደ 6424 ይላኩ!
💁♂️ በቀን 2ብር ብቻ፤ ለ3 ቀናት በነፃ!
ለተጨማሪ መረጃ 👉 https://www.businessexcel.et
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
❤ 23👍 23🥰 4😢 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
✴️ የ41ኛው ዙር አድማስ ዲጂታል ሎተሪ አሸናፊዎች ታወቁ!
አሸናፊዎች እንኳን ደስ አላችሁ🎉🎉
💁♂️ 42ኛው ዙር ቀጥሏል፤ በቴሌብር ወይም ወደ 605 A ብለው በመላክ በ10 ብር ዕድልዎን ይሞክሩ!
🍀 ዕድል ከእርስዎ ጋር ትሁን!
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት እና ኢትዮ ቴሌኮም በአጋርነት
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
❤ 38👍 20🙏 5😁 2😡 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
ክቡር አምባሳደር መሀመድ ድሪር የሞባይል ቴሌፎን አገልግሎትን መርቀው በከፈቱበት ጊዜ!
ግንቦት 19 ቀን 1991 ዓ.ም
አዲስ አበባ
#ትውስታ
#throwbackthursday
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
👍 46❤ 24😁 1
