ru
Feedback
TIKVAH-MAGAZINE

TIKVAH-MAGAZINE

Открыть в Telegram

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። #ኢትዮጵያ ያግኙን +251913134524

Больше
2025 год в цифрахsnowflakes fon
card fon
194 515
Подписчики
-1024 часа
-967 дней
-81530 день
Архив постов
እስራኤል ለሶማሊላንድ የሃገርነት እውቅና የሰጠች የመጀመሪያዋ ሃገር ሆነች። እስራኤል ዛሬ ለሶማሊላንድ የሃገርነት እውቅናን በይፋ ሰጥታለች። ላለፉት 30 አመታት የሃገርነት እውቅና ለማግኘት ስትዳክር የነበረችው ሶማሊላንድ በመጨረሻም ሙከራዋ ተሳክቶ ከእስራኤል የሃገርነት እውቅና አግኝታለች። የእስራኤል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳር እስራኤል እና ሶማሊላንድ የሙሉ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን ለመጀመር፣ አምባሳደሮችን ለመመደብና ኤምባሲዎችን ለመክፈት መስማማታቸውን አስታውቀዋል። የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኔያሁ ከሶማሊላንዱ ፕሬዚዳንት መሐመድ አብዱላሂ ጋር የተነጋገሩ ሲሆን እውቅናው ታሪካዊ ነው ብለውታል። ኔታኔያሁ ዛሬ ሶማሊላንድን እንደ ነፃ እና ሉዓላዊ ሃገር እውቅና መስጠታቸውን አውጀዋል። እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና የሰጠችው አመት ከፈጀ ንግግር በኋላ መሆኑንም አስታውቃለች። 👋   |   @tikvahethmagazine
Показать все...
127👍 58🤣 26👏 5👎 4🤝 4🤔 3🤬 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
ሩሲያ ልዩ ክህሎት እና ችሎታ ያላቸው የውጪ ሃገር ዜጎች በሃገሯ እንዲኖሩ የሚያስችል ፕሮግራም ይፋ አድርጋለች። ለሩሲያ ኢኮኖሚ ጉልህ ሚና ማበርከት የሚችሉና ልዩ ክህሎት እንደዚሁም ችሎታ ያላቸው የውጪ ሃገር ዜጎች በቋሚነት በሩሲያ እንዲኖሩ ፕሬዚዳንት ፑቲን በባለፈው የፈረንጆቹ ታህሳስ 2 አዋጅ ፈርመዋል። ይህ የሩሲያ የቋሚ መኖሪያ የሚሰጣቸው ሰዎች: ➡️ በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ስኬታማ የሆኑ ሳይንቲስቶች ➡️ ልዩ ችሎታና ክህሎት ያላቸው ሰዎች ➡️ 10 ሚሊየን ሩብል ገቢ ያለው ስራ ፈጣሪዎች ➡️ ስኬታማ የስፖርት ሰዎች ➡️ ጥሩ የትምህር ውጤት ያላቸው ተማሪዎች ➡️ ለሩሲያ የመከላከያ እና ደህንነት ዘርፍ አስተዋፅኦ ያደረጉ ሰዎችና ➡️ የፈጠራ ኢንዱስትሪ ተወካዮች ናቸው። ሩሲያ የደህንነት እና የተቀመጡትን ምዘናዎች ለሚያሟሉ የውጪ ሃገር ዜጎች ቋሚ መኖሪያ እንደምትሰጥ ስትገልፅ የውጪ ሃገር ክህሎቶችንም ለመሳብ ይጠቅማል ብላለች። ከዚህ በፊት የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በአካባቢ ጥበቃ አስተዋፅኦ ላደረጉ ሰዎች የ10 አመት የመኖሪያ ፈቃድ እንደምትሰጥ መግለጿ ይታወሳል። 👋   |   @tikvahethmagazine
Показать все...
71👏 22🤣 5🔥 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
 በመሀል ሳር ቤት     ከቴምር ፕሮፐርቲ ➤ 100% ለሚከፍሉ 35% ቅናሽ 👉 ባለ 2 መኝታ = 81ካሬ = 5.7ሚሊዮን 👉 ባለ 2 መኝታ = 106ካሬ = 6.3ሚሊዮን 👉 ባለ 3 መኝታ = 143ካሬ = 10.2ሚሊዮን 👉 ባለ 3 መኝታ = 153ካሬ = 10.9ሚሊዮን ከሌሎች የካሬ አማራጭ ጋ ➤ በ20% ቅድመ ክፍያ (በግንባታ ሂደት ለሚከፍሉ) 👉 81ካሬ = ሙሉ ክፍያ = 9.3ሚሊዮን                  ቅድመ ክፍያ = 20% (1.8ሚሊዮን) 👉 106ካሬ = ሙሉ ክፍያ = 12.1ሚሊዮን                  ቅድመ ክፍያ = 20% (2.4ሚሊዮን) 👉 143ካሬ = ሙሉ ክፍያ = 15.7ሚሊዮን                  ቅድመ ክፍያ = 20% (3.1ሚሊዮን) 🌴 ቀሪውን 80%፤ በግንባታ ሂደት፤ ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ፤ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት። 🌴በተጨማሪም በአዋሬ በተለያዩ የካሬ አማራጭ አፓርትመንቶችን እኛ ጋ ያገኛሉ ለበለጠ መረጃ 0938262649
Показать все...
5
Фото недоступноПоказать в Telegram
በሪልስቴት ግንባታ ዘርፍ ውስጥ አንጋፋ * የሀገር ውስጥ እና የውጭ አልሚዎች * ኮንትራክተሮች እንዲሁም * በተለያየ መስሪያ ቤት ውስጥ በማህበር ተደራጅተው ቤት መገንባት የሚፈልጉ ቤት ሰሪዎች እናንተን ውድ ባለንብረቶች በእጅዎ ፕሮፐርቲስ የሞባይል አፕሊኬሽን ሱፐር ፕላትፎርም ውስጥ እየጠበቋችሁ ይገኛሉ። ይዞታችሁን በትክክለኛ መረጃ መዋቅር ውስጥ በማስገባት ከልዩ ልዩ አልሚዎች ጋር ልናገናኛችሁ ሙሉ ዝግጅታችን ያጠናቀቅን ሲሆን አሁንም በጋራ መገንባት  ፍላጎት ያላችሁ ባለይዞታዎች ንብረቶቻችሁን ይዛችሁ ቅረቡ።በዚህ ትልቅ የ አብሮ ማልማት ግንባታ ፕሮግራም ውስጥ ተሳትፎ ማድረግ ብልህነት ነውና ይፍጠኑ። ለበለጠ መረጃ ☎️ 0990494984 0990464684 የሞባይል መተግበሪያውን ያውርዱና ይቀላቀሉን 👉https://beijoholding.com/
Показать все...
11👏 2
Фото недоступноПоказать в Telegram
ከ100 የሚበልጡ ስደተኞች በሜድትራንያን ባህር ላይ ህይወታቸው አለፈ። 117 ሰዎችን ጭኖ ከሊቢያ በመነሳት አውሮፓ ለመድረስ የሞከረ መርከብ ከሰጠመ በኋላ 116 ሰዎች ሲሞቱ በህይወት የተረፈው አንዱ ብቻ ነው። አደጋው ባለፈው ሳምንት ማጋጠሙ የተዘገበ ሲሆን በህይወት የተረፈው ግለሰብ ወደ ሆስፒታል መወሰዱ ተነግሯል። በህይወት የተረፈው ግለሰብ የተገኘው አደጋው ከደረሰ ከሁለት ቀናት በኋላ ነው ሲባል ያገኙት በእንጨት በተሰራ ጀልባ አሳ የሚያጠምዱ ቱኒዛውያን ናቸው። መርከቧ ከሊቢያ ተነስታ ጥቂት እንደተጓዘች ድጋፍ እንደሚያስፈልጋት መልዕክት ብትልክም በሳተላይትም በአየር ፍለጋም ልትገኝ አልቻለችም። በህይወት የተረፈው ግለሰብ ከሊቢያ ጥቂት እንደተጓዙ መጥፎ የአየር ንብረት መፈጠሩን ገልጿል። በወቅቱ በሰዓት 40 ኪሎ ሜትር የሚነፍስ ነፋስ ነበር ሲባል አደጋውም በዚህ ምክንያት እንደደረሰ ታምኗል። ዘገባው የዴይሊ ኤክስፕረስ ነው። 👋   |   @tikvahethmagazine
Показать все...
😢 98 19💔 9🕊 1
አሜሪካ በናይጄሪያ አይኤስ አይኤስን ኢላማ ያደረገ የአየር ጥቃቶችን ፈፅማለች። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትዕዛዛቸው መሰረት በናይጄሪያ በሚገኙት የእስላሚክ ስቴት ቡድኖች ላይ ጥቃት መፈፀሙን አስታውቀዋል። የአሜሪካ ጦር የአፍሪካ ማዘዣ የአየር ጥቃቱ የተፈፀመው ከናይጄሪያ በቀረበ ጥያቄ ነው ቢልም ይህንን መልዕክት ከማህበራዊ ትስስር ገጹ በኋላ ላይ አንስቶታል። ፕሬዚዳንት ትራምፕ " እንደ ጦር አዛዥነቴ በእኔ ውሳኔ አሜሪካ ዛሬ ለበርካታ አመታት ይቅርና በክፍለ ዘመናት ባልታየ መልኩ ክርስቲያኖችን ቀዳሚ ኢላማ በሚያደርገው በሰሜን ምዕራብ በሚገኘው የአይኤስ አይኤስ አሸባሪ ላይ ከባድ ጥቃት ፈፅማለች" ብለዋል። ትራምፕ አሜሪካ እስላሚክ ሽብርተኝነት እንዲያብብ አትፈቅድም ያሉ ሲሆን የሞቱትን አሸባሪዎች ጨምሮ ለሁሉም መልካም የገና በዓልም ብለዋል። ዶናልድ ትራምፕ ከወራት በፊት ክርስትና በናይጄሪያ የህልውና ስጋት ገጥሞታል በማለት አሜሪካ ወታደራዊ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል ተናግረው ነበር። የፔንታጎን ኃላፊው ናይጄሪያ ላደረገችው ድጋፍ ሲያመሰግኑ የናይጄሪያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጥቃቱ የአሜሪካና የናይጄሪያ የደህንነት ትብብር ውጤት ነው ብሏል። ዘገባው የሮይተርስ ነው። 👋   |   @tikvahethmagazine
Показать все...
3.09 KB
👏 105 44🤣 27👎 9🤔 5
በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ሲፈለግ የነበረ ኤርትራዊ ለኔዘርላንድስ ተላልፎ ተሰጠ። በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ተይዞ የቆየው የ41 አመቱ ኤርትራዊ ዜጋ ኪዳኔ ዘካሪያስ ለኔዘርላንድስ ተላልፎ ተሰጥቷል። የኔዘርላንድስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ ኪዳኔ ከሊቢያ ወደ አውሮፓ የሚጓዙ ስደተኞች ላይ ጥሰት ከመፈፀሙ በተጨማሪ ሰዎችን በማዘዋወር፣ የወንጀል ቡድንን በመደገፍ እና ፆታዊ ጥቃቶችን በመፈፀሙ ሲፈልገው ነበር። ግለሰቡ በኢትዮጵያ የፍርድ ሂደት ላይ ሳለ ካመለጠ በኋላ በ2021 በአለም አቀፍ ደረጃ ተፈላጊ ከነበሩ ሰዎች መካከል ገብቷል። ኪዳኔ ዘካሪያስ በ2023 የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በመራችው ኦፕሬሽን በሱዳን የተያዘ ሲሆን ኤምሬቶች በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ተጠያቂ አድርጋዋለች። የእስር ጊዜውን መጨረሱን ተከትሎም ለኔዘርላንድስ ተላልፎ ተሰጥቷል። ግለሰቡ በርካታ ኤርትራውያን ስደተኞችን በማሰቃየት በዋነኝነት በኔዘርላንድስ ካሉ ቤተሰቦቻቸው ገንዘብ ይቀበል ነበር ተብሏል። በተጨማሪ በያዛቸው ሰደተኞች መካከል የእግር ኳስ ጨዋታ በማድረግ የተሳሳተ እንደሚገደልና ያሸነፈው ቡድን ከተሸናፊው ቡድን ሴት በመምረጥ የወሲብ ጥቃት እንዲፈፅሙ እንደሚደረግ ተነግሯል። ኪዳኔ በ2021 በኢትዮጵያ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ተከሶ ክስ ላይ እያለ ያመለጠ ሲሆን በሌለበት በኢትዮጵያ የእድሜ ልክ እስር ተፈርዶበታል። ኪዳኔ ከወራት በፊት በኔዘርላንድስ ፍርድ ቤት ከቀረበው ዋሊድ ከተባለ ወንጀለኛ ጋር በሰዎች ዝውውርና ማሰቃየት የተከሰሰ ሲሆን በዋሊድ ላይ የኔዘርላንድስ መርማሪዎች የ20 አመት እስር ውሳኔ መጠየቃቸው ይታወሳል። የዋሊድ ጠበቆች ኪዳኔ በፍርድ ቤቱ በምስክርነት እንዲቀርብ የጠየቁ ሲሆን የመጨረሻ ውሳኔ በፈረንጆቹ ጥር 27 ይሰጣል። 👋   |   @tikvahethmagazine
Показать все...
👍 27 21👏 8🤣 2🙏 1
00:37
Видео недоступноПоказать в Telegram
🌟🌟🌟ታላቅ የገና በዓል ቅናሽ በካሬ 78,000 ብር ✅እንዲሁም ሙሉ ክፍያ ለሚከፊል በካሬ 54,800 🔷 በ10 % ቅድመ ክፍያ 🔷 50 %  የባንክ ብድር  የተመቻቸለት 📍Location እንግሊዝ ኢንባሲ አጠገብ  ውብ እይታ (Top View) ያላቸው ቤቶች በሽያጭ ላይ እንገኛለን 👉ከባለ 2 መኝታ- ባለ4 መኝታ ✅ ህንፃው ላይ ያሉ ተጨማሪ አገልግሎትች   ‎👉5 ሰፋፊ ሊፍት /elevator   ‎👉የቆሻሻ መጣያ/garbage chute   👉አውቶማቲክ ጀኔረተር/ automatic generator    ‎👉ሰገነት/terrace    ‎👉የመኪና ማቆምያ/car parking     👉 ጂም , እስፖ we    👉 የዋና ገንዳ    👉 የልጆች መጫወታ ✨ባለ 2 መኝታ ‎           138     ካሬ ‎           157.3   ካሬ ‎           163.6   ካሬ ‎ ✨ባለ 3 መኝታ            152.4  ካሬ            158.1  ካሬ ‎           187.6  ካሬ            211.5  ካሬ ‎ ✨ባለ 4 መኝታ            240.7 ካሬ ‎           258.4 ካሬ ‎        📞 ለበለጠ መረጃ ይደውሉ ‎         0973559591 0919489575              Telegram -@Homef17                https://t.me/lijhop7
Показать все...
7.49 MB
10
Фото недоступноПоказать в Telegram
ቱርኪዬ በአዲስ አመት ጥቃት ሊያደርሱ ነበር ያለቻቸውን 115 የአይኤስ አይኤስ አባላትን ማሰሯን አስታወቀች። የቱርኪዬ የደህንነት ኃይሎች በገና እና አዲስ አመት በዓላት ጥቃት ሊፈፅሙ ነበር ያሏቸውን ከ100 በላይ የአይኤስ አይኤስ አባላትን ማሰራቸውን ገልፀዋል። ቱርኪዬ በ124 ቦታዎች ዘመቻ ካደረገች በኋላ ተጠርጣሪዎቹን መያዟን አስታውቃለች። ቱርኪዬ ኦፕሬሽኑን የጀመረችው ሙስሊም ያልሆኑት ላይ ትኩረት ያደረገ ጥቃት በአይኤስ አይኤስ አባላት ሊፈፀም ስለመታቀዱ መረጃ ከደረሳት በኋላ ነው። የጸጥታ ኃይሎች የጦር መሳሪያዎችን ሲይዙ ያልተያዙ ሌሎች ተጨማሪ 22 ተጠርጣሪዎች ስለመኖራቸውና ለመያዝ እየተሞከረ መሆኑን ገልጸዋል። ቱርኪዬ ከሶሪያ ጋር ሰፊ ድንበር መጋራቷ በ2013 በሽብርተኝነት ለፈረጀችው የአይኤስ አይኤስ ጥቃት ተጋላጭ ያደርጋታል። ባለፈው መጋቢት ወር ቱርኪዬ በ47 ግዛቶች በሰራቸው የሁለት ሳምንት ኦፕሬሽን 298 የአይኤስ አይኤስ አባላት ናቸው ብላ የጠረጠረቻቸውን ሰዎች አስራለች። ይኸኛው እስር የመጣው አሜሪካ በሶሪያ የሽብር ቡድኑን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶችን መፈፀም በጀመረችበት ጊዜ ነው። ቱርኪዬ የስጋት ምንጯ የሆነውን የአይኤስ አይኤስ ቡድን በተለያየ መንገድ እየተከላከለች ሲሆን ከ2013-2023 ብቻ ከቡድኑ ጋር ግንኙነት አላቸው ያለቻቸውን ከ19 ሺህ በላይ ሰዎች አስራለች። ዘገባው የአልጄዚራ ነው። 👋   |   @tikvahethmagazine
Показать все...
50👍 47👏 9🕊 7🤣 2🤔 1💔 1
የዓለም ፍጻሜ ተቃርቧል በማለት ሺዎችን ቀስቅሶ፤ ቀኑ ሲደርስ ትንቢቱ ተሯዝሟል ሲል የገለጸው ጋናዊ የዛሬ መነጋገሪያ ሆኖ ውሏል። እራሱን "ነብይ" ብሎ የሚጠራው ጋናዊው ኤቦ ኖኅ ምድር በፈረንጆቹ ከታህሳስ 25 [ዛሬ] ጀምሮ በከባድ ጎርፍ እንደምትጠለቀለቅ እና ፈጣሪ ሰዎችን ከሚያጠፋውና 3 አመት ከሚቆየው ጎርፍ እንዲድኑ መርከብ እንዲሰራ እንዳዘዘው ተናግሮ ነበር። ይህንን ማለቱም ተከትሎ በርካታ ተከታዮቹ ንብረታቸውን በመሸጥ ለእሱ ገንዘብ በመስጠት የመርከብ አገልግሎት ለማግኘት ወደ እሱ አምርተዋል። ኤቦ በመፅሐፍ ቅዱስ ከምናውቀው የኖህ ዘመን ጋር ተመሳሳይነት ያለው ነገር ይፈጠራል ብሎ የተነበየ ሲሆን የሰራው ግን አስር መርከቦችን ነው። የ30 አመቱ ኤቦ መርከቦቹን ሲሰራም ቪዲዮ እየቀረፀ በማህበራዊ ሚዲያዎች ያጋራ የነበረ ሲሆን ከገና እለት ጀምሮ ለተከታታይ 3 አመታት ዝናብ ያለማቋረጥ ይዘንባል ብሎ ነበር። ዛሬ ታህሳስ 25 ግን ምንም ያልተፈጠረ ሲሆን ኤቦ የመርከብ ፕሮጀክቱን እንዲያስፋፋ ፈጣሪ ተጨማሪ ጊዜ እንደሰጠውና ትንቢቱ እንደተራዘመ ገልጿል። ትንቢቱ ለመቼ እንደተራዘመ ያልገለፀው ኤቦ ተከታዮቹ በሰጡት ገንዘብ የ100 ሺህ ዶላር መርሴዲስ መኪና ገዝቷል ተብሏል። ዘገባው የ WION ነው። 👋   |   @tikvahethmagazine
Показать все...
2.42 MB
🤣 448 65😢 14👎 8🤔 5🔥 2🤯 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
ዩኤኢ ከኤም-ፔሳ ጋር በመተባበር የብሎክቼይን ቴክኖሎጂን በአፍሪካ ለማስፋፋት አቅዳለች በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ፕሬዝዳንት ወንድም በሚመራውና 240 ቢሊዮን ዶላር ሀብት ባለው ኩባንያ የሚደገፈው ኤዲአይ ፋውንዴሽን (ADI Foundation) ከኤም-ፔሳ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱ እስከ 2030 ድረስ አንድ ቢሊዮን ሰዎችን የብሎክቼይን ተጠቃሚ የማድረግ እቅድ አካል ሲሆን የብሎክቼይን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ድንበር ተሻጋሪ ክፍያዎችን ቀልጣፋ እና አስተማማኝ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም፥ ከውጭ ሀገር የሚላክን የገንዘብ ልውውጥ (Remittance) ወጪን በእጅጉ የሚቀንስና እንደ ኤም-ፔሳ ያሉ የዲጂታል የክፍያ አማራጮች ዓለም አቀፍ ተደራሽነት እንዲኖራቸው ያስችላልም ነው የተባለው። ኤዲአይ ፋውንዴሽን ዋና መሥሪያ ቤቱን አቡ ዳቢ አድርጎ፣ በአቡ ዳቢ ግሎባል ማርኬት (ADGM) ስር የመጀመሪያውን ይፋዊ የብሎክቼይን ፈቃድ በማግኘት በሕጋዊ መንገድ ስራ የጀመረ ተቋም ነው። ከኬንያ መንግስት ጋር በመተባበር በአፍሪካ የብሎክቼይን ቴክኖሎጂ ማዕከል (Blockchain Hub) ለመገንባት ስምምነት ቀደም ሲል የተፈራረመ ሲሆን ዓላማውም የኬንያን የግብር አሰባሰብ እና የመንግስት አገልግሎቶችን በብሎክቼይን ለማዘመን ነው። አሁን ላይ ኤዲአይ ፋውንዴሽን እና ኤም-ፔሳ የተፈራረሙት ስምምነት በቬነም የሚለማውን የብሎክቼይን የዲጂታል ክፍያ መሠረተ ልማት ከኤም-ፔሳ ሰፊ የደንበኞች መረብ ጋር ለማገናኘት የሚያስችል ነው። ኤም-ፔሳ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ በ7 ሀገራት (ኬንያ፣ ኢትዮጵያ፣ ታንዛኒያ፣ ሞዛምቢክ ዲአርሲ፣ ሌሴቶ እና ግብጽ ) ውስጥ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። ኤዲአይ ፋውንዴሽን እስከ 2030 ድረስ በታዳጊ አገራት የሚገኙ 1 ቢሊዮን ሰዎችን የብሎክቼይን ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዷል። ተቋሙ በጥር 2026 ዋጋው ከዶላር ጋር የተያያዘ ዲጂታል ገንዘብ (Stablecoin) ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል። ይህ ዘገባ የሴማፎር ነው። 👋   |   @tikvahethmagazine
Показать все...
star reaction 2 59👍 14👎 5