uk
Feedback
ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

Відкрити в Telegram

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Показати більше
2025 рік у цифрахsnowflakes fon
card fon
44 133
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
-22730 день
Архів дописів
Фото недоступнеДивитись в Telegram
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ኔታንያሁ በማጭበርበር ወንጀል ይቅርታ ከጠየቁ በኋላ እስራኤላውያን በቴላቪቭ ተቃውሞ አሰሙ የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ የሙስና ክስ ሙሉ በሙሉ ይቅርታ እንዲደረግላቸው ያቀረቡትን አቤቱታ በመቃወም በቴላቪቭ በሚገኘው የፕሬዚዳንት አይዛክ ሄርዞግ መኖሪያ ቤት በቁጣ የተሞሉ እስራኤላውያን ተቃውሞ አሰምተዋል። የ76 አመቱ ኔታንያሁ በስልጣን ዘመናቸው ለረጅም ጊዜ በዘለቀው የሙስና ክስ ፕሬዝዳንታዊ ይቅርታ እንዲደረግላቸው ከጠየቁ ከሰዓታት በኋላ እሁድ ምሽት የተካሄደው ተቃውሞ ጥፋተኛነታቸውን ሳይቀበሉ እና ጸጸታቸውን ሳይገልጽ ነው በሚል ተቃውሞ ተቀስቅሷል። ናአማ ላዚሚን ጨምሮ የተቃዋሚ ህግ አውጪዎች በተቃውሞው ላይ በደርዘን የሚቆጠሩ አክቲቪስቶች ተቀላቅለዋል።- “ይቅርታ ማለት ባናና ሪፐብሊክ” ነው በሚል መፈክር ከሄርዞግ የግል ቤት በራፍ ላይ በመሰብሰብ የይቅርታ ጥያቄውን ውድቅ እንዲደረግ ጠይቀዋል። አንድ ተቃዋሚ እንደ ኔታንያሁ ብርቱካን የእስር ቤት ልብስ በሱፍ ለብሶ ሲታይ ሌሎች ደግሞ ከትልቅ የሙዝ ክምር ጀርባ እና በላዩ ላይ “ይቅርታ” የሚል ምልክት ፅፈው በኔታንያሁ ላይ ቁጣቸውን ገልፀዋል። ኔታንያሁ ይህቺን አገር እንዴት እንዳፈረሱ ዋጋ ሳይከፍሉ፣ ምንም ዓይነት ኃላፊነት ሳይወስዱ ችሎቱ ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ እየጠየቁ ነው ሲል ታዋቂውዋ ፀረ-መንግሥት አክቲቪስት ሺክማ ብሬስለር ተናግራለች። አክላም የእስራኤል ሰዎች አደጋ ላይ ያለውን ነገር ይገነዘባሉ፣ እናም ይህ ችግር በእርግጥ የአገራችን የወደፊት እጣ ፈንታ ነው ብላለች። የሀገሪቱ የረጅም ዓመታት ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ በሙስና፣ በጉቦ፣ በማጭበርበር እና እምነትን በመጣስ ክሶች ላይ ለአምስት ዓመታት ያህል ፍርድ ቤት ቀርበዋል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
😁 25 14👍 12
ሲንጋፖር ባለፉት ሁለት ቀናት በአደንዛዥ እፅ ወንጀሎች ሶስት ሰዎችን በስቅላት  ቀጣች ሲንጋፖር ባለፈው ሳምንት በአደንዛዥ ዕፅ ወንጀሎች ሶስት ሰዎችን በስቅላት የቀጣች ሲሆነ ዘንድሮ በአጠቃላይ ተግባራዊ የተደረገዉ የሞት ቅጣትን 17 አድርሶታል፡፡ ከ2003 ዓመት ወዲህ ከፍተኛ ተደርጎ ተመዝግቧል። ይህዉ ቅጣት ተግባራዊ የሆነዉ በአደንዛዥ ዕፅ ወንጀሎች ላይ የሞት ቅጣትን በመቃወም ሕገ መንግሥታዊ ውዝግብ ሊሰማ አንድ ሳምንት ሲቀረው ነው። ሲንጋፖር በደቡብ ምስራቅ እስያ ከሚገኙ ሀገራት ለአደንዛዥ ዕፅ ወንጀሎች አስፈላጊ መከላከያ ናቸው ስትል በዓለም ላይ በጣም ከባድ የፀረ-አደንዛዣ እጽ ህጎች አሏት።በህገወጥ የአደንዛዣ እጽ ማዘዋወር ወንጀል የተከሰሰ ማንኛውም ሰው መሸጥ ፣ መስጠት ፣ ማጓጓዝ ወይም ማስተዳደርን ህጉ ያጠቃልላል፡፡ ከ 15 ግራም በላይ ዲያሞርፊን ፣ ከ30 ግራም በላይ ኮኬይን ፣ ከ250 ግራም በላይ ሜታምፌታሚን እና 500 ግራም በላይ ካናቢስ በሲንጋፖር የሞት ፍርድ ያስቀጣል፡፡ ሕገ መንግሥታዊ ጥያቄውን ያቀረቡት ሰባት አክቲቪስቶች የሲንጋፖር አስገዳጅ የሞት ቅጣት ሕገ-መንግሥታዊ የህይወት መብቶችን እና የህግ ጥበቃን የጣሰ ነው ሲሉ ይከራከራሉ።ሕገ መንግሥቱ ‹‹ማንኛውም ሰው በሕግ ከተደነገገው በቀር ሕይወቱን ወይም ነፃነቱን አይገፈፍም›› ይላል።የሲንጋፖር አረመኔያዊ የአደንዛዥ ዕፅ ቁጥጥር አገዛዝ በአለም መድረክ ላይ ከፍተኛ ተቃዉሞ እየገጠመዉ ይገኛል፡፡የአገር ውስጥ አክቲቪስት ቡድን ትራንስፎርሜቲቭ ጀስቲስ ኮሌክቲቭ በበኩሉ በአደንዛዥ እጽ ወንጀል ሰዎችን እየገደሉ ከሚገኙ ጥቂት ሀገራት አንዷ ሲንጋፖር ነች ብሏል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
👏 15 9
Фото недоступнеДивитись в Telegram
ታላላቅ ጦርነቶች በመቀስቀሳቸው የዓለም የጦር መሳሪያ አምራቾች ገቢ ጨመረ በስቶክሆልም ዓለም አቀፍ የሰላም ምርምር ኢንስቲትዩት (SIPRI) ባወጣው አዲስ መረጃ መሠረት በ100 ትልልቅ ዓለም አቀፍ የጦር መሣሪያ አምራች ኩባንያዎች ከጦር መሣሪያ እና ከወታደራዊ አገልግሎት ሽያጭ የተገኘው ገቢ በ2024 ወደ 679 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል። የጋዛ እና የዩክሬን ጦርነቶች፣ እንዲሁም አለም አቀፋዊ እና ክልላዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች እና ከፍተኛ ወታደራዊ ወጪዎች መጨመር ኩባንያዎቹ ከወታደራዊ እቃዎች እና አገልግሎቶች ሽያጭ የሚያገኙት ገቢ ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር በ5.9 በመቶ ጨምሯል። ከአለም አቀፉ እድገት ትልቁን ድርሻ የሚይዙት በአውሮፓ እና በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ያሉ ኩባንያዎች ናቸው ፣ ከኤሺያ እና ኦሺያኒያ በስተቀር በሁሉም ክልሎች ከዓመት አመት ጭማሪዎች ነበሩ ፣ በቻይና የጦር መሳሪያ ኢንዱስትሪ ውስጥ ያሉ ጉዳዮች የአከባቢውን አጠቃላይ ድምር ዝቅ አድርገውታል። ሎክሄድ ማርቲን፣ ኖርዝሮፕ ግሩማን እና ጄኔራል ዳይናሚክስ በዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ከፍተኛ የጦር መሳሪያ ገቢ በ2024 ዓመት በማግኘት በ3.8 በመቶ እድገት በማስመዝገብ 334 ቢሊየን ዶላር ደርሷል።በደረጃ አሰጣጡ ከ39 የአሜሪካ ኩባንያዎች 30 ያህሉ ገቢያቸውን ጨምሯል። የኤሎን ማስክ ስፔስ ኤክስ የጦር መሳሪያ ገቢ ከ 2023 ጋር ሲነጻጸር በእጥፍ ጨምሯል። ገቢው 1.8 ቢሊዮን ዶላር ከደረሰ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአለም አቀፍ ከፍተኛ ወታደራዊ አምራቾች ዝርዝር ውስጥ ስፔስ ኤክስ ተካቷል።ሩሲያን ሳይጨምር ከ100 ምርጥ የጦር መሳሪያ ኩባንያዎች ውስጥ በአውሮፓ ከሚገኙት ከ26ቱ መካከል 23ቱ የጦር መሳሪያ እና መሳሪያ ሽያጭ ገቢ ጭማሪ አስመዝግበዋል። አጠቃላይ የጦር መሳሪያ ገቢያቸው በ13 በመቶ ጨምሮ ወደ 151 ቢሊዮን ዶላር አድጓል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
25🕊 9💔 7🤔 4🔥 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
5
AA1Rsyks.webp0.48 KB
Фото недоступнеДивитись в Telegram
የመጀመሪያዋ ከማርበርግ ቫይረስ ያገገመችው የ15 ዓመት ታዳጊ ከቫይረሱ ነፃ በመሆኗ ከህክምና ማአከል ወጣች የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንደሻው ሽብሩ እንደገለፁት ታማሚዋ የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምልክት በማሳየቷ ህክምና ሲደረግላት ቆይቶ፣ በላቦራቶሪ ምርመራ ከቫይረሱ ነፃ መሆኗ በመረጋገጡ ከህክምና ማዕከል እንድትወጣ መደረጉን አስረድተዋል። የበሽታው ታማሚ ታዳጊ በአምላክ ምትኩ 15 ዓመቷ ሲሆን በሽታው መኖሩ በላቦራቶሪ ምርመራ ተረጋግጦ፣  በተደረገላት ህክምና ከበሽታው ማገገም ችላለች፡፡ የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምልክቱ በሚታይበት ወቅት ወዲያውኑ ወደ ጤና ተቋም የሚመጡ አካላት የማገገም ዕድላቸው ሰፊ በመሆኑ ሁሉም ሰው ሳይዘናጋ የቫይረሱ  ምልክቶች ሲኖሩ ፈጥኖ ወደ ህክምና ማዕከል መምጣት በሽታውን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ያስችላል መባሉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል። በቀጣይ ቀናት ከማርበርግ ቫይረስ በሽታ አገግመው የሚወጡ ታማሚዎች ስለመኖራቸውም የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ገልጿል። በትግስት ላቀው #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
60👍 18🤔 2👎 1
የመጀመሪያዋ ከማርበርግ ቫይረስ ያገገመችው የ15 ዓመት ታዳጊ ከቫይረሱ ነፃ በመሆኗ ከህክምና ማአከሉ ወጣች የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንደሻው ሽብሩ እንደገለፁት ታማሚዋ የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምልክት በማሳየቷ ህክምና ሲደረግላት ቆይቶ፣ በላቦራቶሪ ምርመራ ከቫይረሱ ነፃ መሆኗ በመረጋገጡ ከህክምና ማዕከል እንድትወጣ መደረጉን አስረድተዋል። የበሽታው ታማሚ ታዳጊ በአምላክ ምትኩ 15 ዓመቷ ሲሆን በሽታው መኖሩ በላቦራቶሪ ምርመራ ተረጋግጦ፣  በተደረገላት ህክምና ከበሽታው ማገገም ችላለች፡፡ የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምልክቱ በሚታይበት ወቅት ወዲያውኑ ወደ ጤና ተቋም የሚመጡ አካላት የማገገም ዕድላቸው ሰፊ በመሆኑ ሁሉም ሰው ሳይዘናጋ የቫይረሱ  ምልክቶች ሲኖሩ ፈጥኖ ወደ ህክምና ማዕከል መምጣት በሽታውን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ያስችላል መባሉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል። በቀጣይ ቀናት ከማርበርግ ቫይረስ በሽታ አገግመው የሚወጡ ታማሚዎች ስለመኖራቸውም የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ገልጿል። በትግስት ላቀው #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
👍 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
አሳዛኝ መረጃ ተወዳጁ ኮሜዲያን ወንድወሰን አዉራሪስ በልብ ህመም ምክንያት ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል። ነፍስ ይማር፡ ለቤተሰቦቹና ወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን ይስጥልን። #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
💔 105😭 37😱 23 12🤔 1
በዛሬው እለት በደረሰ የትራፊክ አደጋ በአንድ ዶልፊን የነበሩ 11 ሰዎች ሰዎች ህይወቱ አለፈ። ከአደጋው የተረፈ ተሳፋሪ የለም በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጉቢ ቦርደዴ ወረዳ በዛሬው እለት አስር ሰዓት ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ አንድ ዶልፊን ያሳፈራቸው አስራ አንድ ሠዎች ህይወታቸው ማለፉን የምዕራብ ሐረርጌ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ አስታውቋል። የምዕራብ ሐረርጌ ዞን  ፖሊስ ዋና መምርያ የትራፊክ ደሕንነት ና ቁጥጥር አስተባባሪ ምክትል ኢንስፔክተር ዳኙ ሶሪ ለብስራት ሬዲዬ እንደተናገሩት ዛሬ ህዳር 20 ቀን 2018 ዓም መነሻውን ከሚኤሶን ከተማ ያደረገ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3-96835 ኦሮ ዳልፊን የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ዘጠኝ ተሣፋሪዎችን አሳፍሮ ወደ አዋሽ ከተማ ሲጓዝ  ነበር። ተሸከርካሪው በተቃራኒ መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ጅቡቲ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3-ኤ-11805 ኢቲ  የነዳጅ ማመላለሻ ቦቴ  ቁቢ ቦርደዴ ወረዳ ጨቱ ቀበሌ በተባለ ስፍራ ፊት ለፊት ተጋጭተዋል። በአደጋው በዶልፊኑ ውስጥ የነበሩ አሽከርካሪውን እና ረዳቱን ጨምሮ የስምንት ወንዶችና የሶስት ሴቶች በአጠቃላይ ተሽከርካሪው ውስጥ የነበሩ ሰዎች በሙሉ ህይወታቸው ማለፉን ገልፀዋል። የአደጋው መንሴ የዶልፊኑ ተሽከርካሪው መስመሩን ለቆ ወደ ተቃራኒ አቅጣጫ በመግባቱ ና ፊት ለፊት ከነዳጅ ጫኝ ቦቴው ጋር በመጋጨቱ ሲሆን የነዳጅ ቦቴ አሽከርካሪው ለግዜው ተሰውሯል።ፖሊስ ከተሽከርካሪው ውስጥ የመንጃ ፈቃዱን ና ሌሎች መረጃዎችን በማግኘቱ ክትትል ላይ መሆኑን ገልፀዋል። የሟቾች አስክሬን ለምርመራ ወደ ሆስፒታል የተላከ ሲሆን በአንድ አደጋ ሙሉ ተሳፋሪ ህይወቱ ያለፈበት አጋጣሚ ከዚህ ቀደም የተመዘገበ እንደሌለ ምክትል ኢንስፔክተር ዳኙ ሶሪ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል። በኤደን ሽመልስ #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
💔 55 33😭 24😱 15👍 1😁 1
ራሚስ ባንክ በ2017 በጀት ዓመት ከ400 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ ራሚስ ባንክ በበጀት ዓመቱ  ከ400 ሚሊየን ብር በላይ ጠቅላላ ገቢ በማስመስገብ ወደ ትርፍ መሸጋገሩን የራሚስ ባንክ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አሊ አህመድ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል። ከኢትዮጵያ ብሄራዊ  ባንክ  ፈቃድ አግኝቶ ወደ ስራ የገባው ባንኩ በ6ሺህ 325 ባለአክሲዮኖች በ2.1 ቢሊዮን የተመዘገበ ካፒታል ይዞ ወደ ስራ የገባ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ ባንክ ነው። አቶ አህመድ ከጣቢያች ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት ባንኩ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ጀምሮ ጠቅላላ ሀብቱ በማሳደግ ከ4.2 ቢሊየን ብር በላይ አድርሷል ሲሉ ተናግረዋል። ከባለፈው በጀት ዓመት ካስመዘገበው ጠቅላላ ገቢ 3 ሺህ 726 በመቶ  እድገት ያሳየ ሲሆን የተጣራ ትርፍም በ101 በመቶ ማሳደግ ችሏል። በተጨማሪም ባንኩ 20 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ያሰባሰበ ሲሆን 47 ቅርንጫፎችን ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል። በተጠናቀቀው በጀት አመት ጠቅላላ ወደ 352 ሺ ደንበኞችን በማፍራት የደንበኞቹን ቁጥር በ 93 በመቶ አሳድጓል። የዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ፣የኢንተርኔት ባንኪንግ፣ ዋሌት እና ኢ-ሙራበሃ ያሉ ዘመናዊ የዲጂታል ባንክ አማራጮችን በፍጥነት  በመተግበር ላይ ይገኛል። በሳምራዊት ስዩም #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
👍 18 17👎 5🤔 2
የደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ (UNISA) በኢትዮጵያ 12ኛውን የምርቃት ስነስርዓት አካሄደ የደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ (ዩኒሳ) በሀይሌ ግራንድ ሆቴል 12ኛውን የምርቃት ስነስርዓት በዛሬው እለት በድምቀት አክብሯል። 👉ዩኒሳ 64 ተማሪዎች ያስመረቀ ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል 58ቱ የፒኤችዲ (PHD) ዲግሪ ያገኙ ናቸው። በምርቃቱ ላይ የዩኒሳ ፕሪንሲፓል እና ምክትል ቻንስለር ፕሮፌሰር ፑሌንግ ሌንካቡላ፣ የኢትዮጵያ መግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የደቡብ አፍሪካ ሪፐብሊክ ኤምባሲ ተወካዮች እና የዩኒሳ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል። የዩኒሳ የኢትዮጵያ ሪጅናል የትምህርት ማዕከል እኤአ በ2004 በኢትዮጵያ እና በደቡብ አፍሪካ መንግስታት መካከል በተፈረመው ስምምነት እና ከዚያም በኋላ ዩኒቨርሲቲው የሰው ኃይል ልማትን ለማፋጠን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በፈረመው ስምምነት መሰረት እኤአ በ2007 ነበር ስራውን የጀመረው። ይህ ሽርክና የአፍሪካ ሀገራት በትምህርት አማካኝነት የጋራ የልማት ችግሮችን ለመፍታት የሚተባበሩበት የደቡብ ለደቡብ  (south-south) ትብብር ህያው ማሳያ መሆኑን ብስራት ሬድዮ ሰምቷል። ከደቡብ አፍሪካ ውጭ ብቸኛው የዩኒሳ ማዕከል የሆነው የኢትዮጵያ ሪጅናል የትምህርት ማዕከል፣ ለኢትዮጵያውያን የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች ከመግቢያ ጀምሮ እስከ ምርቃት ድረስ አጠቃላይ የአካዳሚክ እና የአስተዳደራዊ ድጋፍ ይሰጣል። ማዕከሉ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ 629 የዶክትሬት እና 382 የማስተርስ ተመራቂዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ 1163 ተማሪዎችን አስመርቋል። አብዛኛዎቹ ተመራቂዎች የዩኒቨርስቲ መምህራን እና ባለሙያዎች ሲሆኑ፣ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዘርፎች በአመራርነት በማገልገል ላይ ይገኛሉ። ዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች የድህረ-ምረቃ ምርምር የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርግ ብስራት ሰምቷል። የአፍሪካ መሪ የርቀት እና የኢ-ለርኒንግ (ODel) ተቋም የሆነው ዩኒሳ፣ በ152ኛ ዓመቱ በመላው አህጉሪቱ ተደራሽ እና ጥራት ያለው ት/ትን በመስጠት ፈር ቀዳጅ ሆኖ ቀጥሏል። የኔልሰን ማንዴላን "ትምህርት ዓለምን ለመለወጥ ልትጠቀምበት የምትችለው ከሁሉ የላቀ ኃይለኛ መሳሪያ ነው" የሚለውን ንግግር በማስተጋባት፣ ዩኒሳ በት/ት አማካኝነት የኢትዮጵያን የለውጥ ጉዞ ለመደገፍ በላቀ ቁርጠኝነት ይሰራል። ሰላማዊ ነጋሲ #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
20👍 3
Фото недоступнеДивитись в Telegram
የማንችስተር ዩናይትድ ከ 18 አመት በታች ቡድን የሊቨርፑል አቻዉን በሜዳዉ 7 ለ 0 ረምርሟል። የ 15 አመቱ ታዳጊ ጄጄ ጋብሬል በጨዋታው ሀትሪክ ሰርቷል። ሽንፈቱ የሊቨርፑል የዋናዉ ቡድን ቀዉስ ወደ ታችኛው ቡድንም ተላለፈ እንዴ ያስብላል። ሊቨርፑል በዋናዉ ቡድኑ ከዚህ ቀደም ዩናይትድን በአንፊልድ 7 ለ 0 አሸንፎት ያዉቃል። #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
😁 29 16👍 1👎 1
ሞባይል ስልክ ቀምቶ ወንዝ ውስጥ የገባው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ ተከሳሽ ካሊድ አህመድ የሞባይል ስልክ ቅምያ ወንጀል በመፈጸም በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ኢምፔሪያል ድልድይ አካባቢ ነው። አንድ ግለሰብ በአካባቢው መንገድ ላይ እየተንቀሳቀሰ ሳለ ተጠርጣሪ ካሊድ አህመድ በፍጥነት ቀርቦ ሞባይሉን ቀምቶ ለመሰወር ሲሞክር በወቅቱ በወንጀል መከላከል ስራ ላይ በነበሩ የአደይ አበባ ስታዲየም አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል መከላከል አባላት ዓይን ውስጥ ገብቷል። የፖሊስ አባላቶቹም ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል ባደረጉት ብርቱ ክትትል ተከሳሽ ወደ ውሀ መውረጃ ድልድይ ውስጥ ገብቶ ቢደበቅም ከአንድ ሠዓት በላይ በፈጀ ፍለጋ ሊያዝ መቻሉን ፖሊስ ገልጿል። ፖሊስም ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ የማስፋት ተግባሩን አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቆ ክስ ተመስርቶበታል ። ህዝባዊ ፖሊስ ምን ጊዜም አስፈላጊውን መስዋዕትነት በመክፈል ለህግ የበላይነት መስፈን እንደሚቆም ያስታወቀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ህብረተሰቡ ለወንጀል ፈጻሚዎች ምቹ በሆኑ አካባቢዎች በቂ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበትም መልዕክቱን አስተላልፏል። ምንጭ:- አአ ፖሊስ #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
👏 19 11😁 10👎 3🙏 2😢 1👀 1
አማራ ባንክ ከታክስ በፊት 655 ሚሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን ገለፀ ባንኩ ይህንን ያስታወቀዉ በዛሬዉ ዕለት ባካሄደዉ የባለአክስዮኖች 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ወቅት ነዉ ። የአማራ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ዮሐንስ አያሌዉ ባንኩ በበጀት ዓመቱ ከታክስ በፊት ያስመዘገበዉ 655 ሚሊዮን ትርፍ ካለፈዉ ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ85 በመቶ ብልጫ እንዳለዉ መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል ። የባንኩ የብድር ክምችት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በ29 በመቶ በማሳደግ ወደ 25.5 ቢሊዮን ብር ማሳደግ ተችላል ። በ2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን በ26 በመቶ በማሳደግ ወደ 31.5 ቢሊዮን ብር ማሳደጉ ተነግሯል ። የባንኩ አጠቃላይ ገቢ በ29 በመቶ በማሳደግ ወደ 5.6 ቢሊዮን ብር መጨመር መቻሉን ዋና ስራ አስፈፃሚዉ ለጠቅላላ ጉባኤዉ ተሳታፊዎች ይፋ ማድረጋቸውን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል። የዲጂታል ባንክ አማራጮችን መሰረተ ልማት ለማስፋፋት ከ134 በላይ አዲስ የኤቲኤም ማሽኞችን ወደ ስራ ማስገባቱ ፣105ሺህ 40 4ኪው አር ኮድ መዘርጋቱ ፣308 በካርድ ክፍያ መፈፀሚያ ፖስ ማሽኖችን ስራ ላይ ማዋሉ እንዲሁም ከ112ሺህ በላይ የኤቲኤም ካርድ ማሰራጨቱ የዲጂታል ባንክ ስነ ምህዳርን በከፍተኛ እያሳደገዉ ነዉ ተብሏል ። የአማራ ባንክ ዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ጋሻዉ ደበበ ቦርዱ ለዘላቂ እድገትና ልቀት ጠንካራ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ በመስጠት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል ። የባንኩ ደንበኞች ቁጥር ወደ 2.4 ሚሊዮን ማደጉ በአገልግሎቱ መተማመን እና እርካታ እያደገ ለመምጣቱ ማሳያ ነዉ ተብሏል ። በመባ ወርቅነህ #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
31👎 11👍 2😭 2👀 1
4🔥 1
የሞባይል ስልክ በሳሙና ውስጥ ሸሽጎ ማረሚያ ቤት ሊያስገባ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ዋለ በዲላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም በአባሎች ጠንካራ የሆነ ፍተሸ ህዳር 18/2018 ዓ/ም ዕለተ ሐሙስ ዘመድ ጥየቃ ከሚገቡ ሰዎች ጋር ሞባይል ስልክ በሳሙና ውስጥ ደብቆ ለማስገባት የሞከረው አስራት አሸናፊ የተባለ ግለሰብ በተደረገ ጠንካራ ፍተሻ እጅ ከፍንጅ ተይዟል። የተቋሙ ኢንስፔክተር ትዕስት ሮቤ እንደተናገሩት ከዘመድ ጠያቂዎች ጋር በመቀላቀል ሞባይል ስልክ ለማስገባት ስሞክር በፍተሻ ተይዞ ወደ ታራሚዎች ሳይገባ መከላከል መቻሉን ገልፀዋል። አክለውም ህብረተሰቡ ከእንደዚህ ዓይነት ድርጊት እንድቆጠቡ እና የማረም ማነጽ ስራን ከሚያሰናክል ተግባር በመጠንቀቅ ታራሚዎች ከሱስ ነፃ እና አምራች ዜጋ ሆነው እንድወጡ የበኩላቸውን ድርሻ እንድወጡ ጥር አቅርበዋል። #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
😁 17 6👏 3👍 1🤔 1🤣 1
Фото недоступнеДивитись в Telegram
አርኤስኤስ በሱዳን ኮርዶፋን የሚገኝ ሆስፒታልን ወደ ወታደራዊ ጦር ማዘዣ መቀየሩ ተሰማ የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሃይሎች (አር ኤስ ኤፍ) ከተማዋን ከተቆጣጠሩ ከአምስት ወራት በኃላ በሱዳን ደቡብ ምዕራባዊ ኮርዶፋን የሚገኘውን የአል ኑሁድ ሆስፒታል ትልቅ ክፍልን ወደ ወታደራዊ ማዘዣ ማእከል እና የጦር ሰፈር ለውጠዋል ሲል የሱዳን ዶክተሮች ኔትወርክ አስታውቋል። መንግስታዊ ያልሆነው ድርጅት እንዳስታወቀው በአርኤስኤፍ እና የሱዳን ጦር ሃይሎች (ኤስኤፍኤ) በአሰቃቂው የሶስት አመት የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት ሆስፒታሉ ለህዝቡ የጤና አገልግሎት በመስጠት ላይ ያለውን ወሳኝ ሚና እንዳይወጣ እየከለከለው ነው ብሏል። ይህ ወታደራዊ አጠቃቀም የህክምና ተቋማትን ደንብ የሚጻረር እና የዜጎችን ህክምና የማግኘት መብት የሚጎዳ ነው ሲል በፌስቡክ ላይ ኔትወርኩ ያወጣው መግለጫ ያሳያል። በከተማው ውስጥ ያሉ አንዳንድ የህክምና ባለሙያዎች ከተማዋን ከመሸሻቸው በፊት ከወታደራዊ ኃይል ጋር በመተባበር ተከስሰዋል። በዚህም ምክንያት ሆስፒታሉ በከባድ የጤና አጠባበቅ ባለሙያዎች እጥረት እየተሰቃየ ነው። በዚህን የተቀሩት የሕክምና አገልግሎቶች በጣም ውስን እና የታካሚዎችን ፍላጎት ማሟላት አልቻሉም ተብሏል። በስምዖን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Показати все...
23💔 9👎 2