ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
Kanalga Telegram’da o‘tish
በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
Ko'proq ko'rsatish2025 yil raqamlarda

50 485
Obunachilar
-624 soatlar
+27 kunlar
+10030 kunlar
Postlar arxiv
=>እነዚህንና ስማቸውን ያልጠራናቸውን ሌሎች ቅዱሳንን ዜና ማንበብ: በስማቸው መልካሙን ማድረግና መዘከር ዋጋው በሰማያት ታላቅ መሆኑን ገድለ አባ ኤሲ እና ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ ይናገራል:: (ማቴ. 10:41, ዮሐ. 4:36, ዕብ. 6:10)
=>አምላከ ከዋክብት ቅዱሳን ከዓመጸኛው ትውልድ ይሰውረን:: በረድኤታቸው ጥላ ጋርዶ: ለበረከታቸው ያብቃን::
=>ታሕሳስ 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ታላቁ አቡነ ኪሮስ
2.አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
3.አባ ዮሐንስ ዘደማስቆ (ሊቁ)
4.አባ ኤሲና ቅድስት ቴክላ
5.ቅዱሳት በርባራና ዮልያና
6.ቅድስት እንባ መሪና
7.አባ ተክለ አልፋ ዘደብረ ድማሕ
8.ቅዱስ ገብረ ማርያም ተአማኒ
9.አባ ያሮክላ ሊቀ ዻዻሳት
10.አቡነ እስትፋሰ ክርስቶስ (ልደታቸው)
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
2.አባ ብሶይ (ቢሾይ)
3.ቅዱሳን 4ቱ እንስሳ (ኪሩቤል)
4.ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ (ከ12ቱ ሐዋርያት)
=>+"+ እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ: እስከ አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ: ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ አይደለምና:: በእምነትና በትእግስትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን::+"+ (ዕብ. 6:10)
<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>
https://t.me/zikirekdusn
''' እንኩዋን ለቅዱሳን *አቡነ ኪሮስ *ዮሐንስ ዘደማስቆ *ሳሙኤል ዘቀልሞን *ተክለ አልፋ *ኤሲ *በርባራ *እንባ መሪና እና *ገብረ ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! '''
=>ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚሁ ቀን የምታከብራቸው ብዙ ቅዱሳን አሏት:: ሁሉን ለመዘርዘር ይከብዳል:: ግን የጥቂቱን ዜና ለበረከት እንካፈል ዘንድ የጌታ ፈቃዱ ይሁንና ስለ እያንዳንዱ በጥቂቱ እናንሳ::
+*" አቡነ ኪሮስ ጻድቅ "*+
=>የጻድቁን ስም የሚጠራ አፍ ንዑድ ነው: ክቡር ነው:: በእውነት የቅዱሱን አባት ክብር ለማግኘት መፋጠን ይበጃል:: አቡነ ኪሮስ የተወለዱት በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን ወላጆቻቸው ነገሥታት ናቸው::
+ተወልደው ባደጉባት ሃገር ቁስጥንጥንያ ገና በልጅነት ምቾት ሳያሳሳቸው መጻሕፍትንና ትሕርምትን ተምረዋል:: ወንድማቸው (ታላቁ ቴዎዶስዮስ) በነገሠባቸው የመጀመሪያ ዓመታት በቤተ መንግስቱ ዙሪያ ግፍ በዝቶ ነበርና አቡነ ኪሮስ ከኃጢአት ለመራቅና ለጌታ ለመገዛት ከከተማው ጠፍተው: አሕጉር አቁዋርጠው ወደ ግብፅ (ገዳመ አስቄጥስ) መጡ::
+እርሳቸውን ለመፈለግ የተደረገው ሙከራ አልተሳካም:: ይባስ ብሎ የንጉሡ ልጅ ገብረ ክርስቶስ ሙሽርነቱን ጥሎ ወደ ሌላ ሃገር መነነ:: "የቅኖች ትውልድ ይባረካል" እንዳለ ቅዱስ ዳዊት አቡነ ኪሮስ ለሙሽራው ገብረ ክርስቶስ አጎቱ ናቸው:: አቡነ ኪሮስ በገዳም ውስጥ የታላቁ አቡነ በብኑዳ ደቀ መዝሙር ሆነው ለዘመናት ቆይተዋል::
+ቅዱስ በብኑዳን አንበሳ በበላው ጊዜ በጣም አዝነው "ለምን ጌታ ሆይ?" በሚል መሬት ላይ ወድቀው አለቀሱ:: "ምክንያቱ ካልተነገረኝ አልነሳም" ብለው ከወደቁበት መሬት ላይ ሳይነሱ ለ40 ዓመታት አልቅሰዋል:: በዚህ ምክንያት ግማሹ አካላቸው አፈር ሆኖ ሣር በቅሎበታል::
ጌታችን ተገልጦ ምክንያቱን ነግሯቸዋል:: አካላቸውንም እንደነበረ መልሶላቸዋል::
+አንድ ቀን ጻድቁ ለቅዱስ በብኑዳ ሞት ምክንያት የሆነው መነኮስ ታንቆ መሞቱን ሰምተው በጣም አዘኑ:: ሱባዔ ገብተው: ፍጹም አልቅሰው: ከጌታም አማልደው: የዛን ኃጥእ ነፍስ ከሲዖል አውጥተዋል:: በሌላ ጊዜ ደግሞ ኃጥአን የሞሉበት አንድ ገዳም በግብጽ ነበርና መቅሰፍት ወርዶ ሁሉንም ባንድ ቀን ሲያጠፋቸው አዩ::
+ጻድቁ በዚህም ምክንያት ለ30 ዓመታት አልቅሰው: ሙታኑን አስነስተው: ንስሃ ሰጥተው: ገዳሙን የጻድቃን: ሕይወታቸውንም የፍቅር አድርገውታል:: ጻድቁ እመቤታችንን ከመውደዳቸው የተነሳ በስዕሏ ፊት አብዝተው ይሰግዱና ያለቅሱ ነበር:: እመ አምላክም ተገልጣ ትባርካቸው ነበር::
+ከዚህ በሁዋላ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ሒደው ለ57 ዓመታት ማንንም ሳያዩ ተጋደሉ:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ (ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና) በየቀኑ ይጐበኛቸው: ቁጭ ብሎም ያወራቸው ነበር::
+በመጨረሻም ጌታ አእላፍ መላእክትን: ጻድቃን ሰማዕታትን: ድንግል እመቤታችንና ቅዱስ ዳዊትን አስከትሎ ወረደ::
+ቅዱስ ዳዊት ቀርቦ እያጫወታቸው: በበገናው እየደረደረላቸው: ከዝማሬው ጣዕም የተነሳ ነፍሳቸው ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ጌታችንም ታቅፎ: ስሞ ይዟቸው አረገ::
+ሥጋቸውን አባ ባውማ ቀበሩት:: የአቡነ ኪሮስ ቁመታቸው ቀጥ ያለ: ጽሕማቸውም የተንዠረገገ ነበር:: እድሜአቸውን ግን መገመት የሚቻል አይመስለኝም:: (ጻድቁ የተወለዱት በዚሁ ቀን ነው)
+*" አባ ሳሙኤል ዘቀልሞን "*+
=>በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን በግብጽ ደብረ ቀልሞን የነበሩ:
*ከዓበይት ጻድቃን የሚቆጠሩ:
*ቀውስጦስ የሚባለውን መልአክ አማልደው ክንፈ ረድኤቱ እንዲመለስ ያደረጉ::
*መልአክን እንኩዋ ማማለድ የቻሉ::
*የታላቁ አባ አጋቶን ደቀ መዝሙር የሆኑ:
*ስለ ቀናች ሃይማኖት የተደበደቡ:
*መናፍቃን አንድ ዐይናቸውን ያጠፉባቸው:
*በፍጹም ትሕርምት የኖሩ:
*እልፍ ደቀ መዛሙርትን ያፈሩ::
*ተአምራትን የሠሩ:
*ደብረ ቀልሞን ገዳምን የመሠረቱና
*እመቤታችንን በፍጹም ልባቸው የወደዱ ቅዱስ አባት ናቸው:: (ዛሬ ዕረፍታቸው ነው)
+*" ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ "*+
=>በ6ኛው መቶ ክ/ዘመን በሶርያ ደማስቆ የተነሳ:
*ፍልስፍናንም: ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንንም ያጠና:
*ስለ ስዕለ አድኅኖ ክብር ከነገሥታቱ ዘንድ የተዋጋ:
*በጦማር (በደብዳቤ) ለዓለም የሰበከ:
*ስለ እመቤታችን ተናገርክ ብለው ቀኝ እጁን የቆረጡት::
*እመ ብርሃን ግን እንደ ገና የቀጠለችለት:
*በበርሃ ውስጥ ለዘመናት በገድልና በጽሙና የኖረ:
*ከ10ሺ በላይ ድርሳናትን የደረሰ:
*ከዐበይት ሊቃውንት የሚቆጠር ቅዱስ አባት ነው:: (ዛሬ ዕረፍቱ ነው)
+*" ቅድስት በርባራ "*+
=>በዘመነ ሰማዕታት (በ3ኛው ክ/ዘ) የነበረች:
*በአረማዊ ንጉሥ አባቷ ጣዖት እንድታመልክ ብትገደድ "እንቢ" ያለች:
*ከባልንጀራዋ ዮልያና ጋር በፍጹም ትእግስት የታገለች:
*የአባቷን ምድራዊ ክብር ንቃ ስለ ክርስቶስ መከራን የተቀበለች:
*በአባቷ እጅ ከቅድስት ዮልያና ጋር የተገደለች:
*እጅግ ብዙ ተአምራትንም የሠራች ቅድስት: ወጣት ሰማዕት ናት:: (ዛሬ ዕረፍቷ ነው)
+" አባ ኤሲ "+
=>በዘመነ ሰማዕታት በግብጽ (ቡጺር) ከደጋግ ክርስቲያኖች የተወለደ:
*ከልጅነቱ ጀምሮ ዓለምን የናቀ:
*በወጣትነቱ የነዳያንና የእሥረኞች አባት የተባለ:
*ቅድስት ቴክላ የተባለችና እመቤታችን የምታነጋግራት እህት የነበረችው:
*ቅዱስ ዻውሎስ ከሚባል ባልንጀራው ጋር ሰማዕታትን በመንከባከብ ያገለገለ:
*በመንፈሳዊ ቅናት ከዻውሎስና ቴክላ ጋር ለሰማዕትነት የቀረበ::
*እጅግ ብዙ መከራዎቸን የተቀበለ::
*ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሱርያል ወደ ሰማይ አሳርጐ ክብረ ቅዱሳንን ያሳየው::
*ቅዱሳንን የሚዘክሩ ሰዎችን ክብር አይቶ የተደነቀና::
*ከብዙ ተከታዮቹና ቅድስት እህቱ ጋር የተሰየፈ ታላቅ ሰማዕት ነው:: (ዛሬ ዕረፍቱ ነው)
+*" ቅድስት እንባ መሪና "*+
=>በዘመነ ጻድቃን በምድረ ግብጽ የተወለደች::
*ከአባቷ ጋር መንና ወደ ወንዶች ገዳም የገባች::
*ወንድ መስላ የወንዶችን ቀኖና በምንኩስና የተቀበለች::
*ያለ አበሳዋ (ወንድ መስላቸው) "ዝሙት ሰርተሻል" ተብላ ወደ በርሃ የተባረረች::
*ያልወለደችውን ልጅ ያሳደገች::
*ያለ ምግብና ውሃ ለ3 ዓመታት የተሰቃየች::
*ብርድና ፀሐይ የተፈራረቀባትና:
*ስታርፍ ክብሯ የተገለጠላት ቡርክት እናት ናት:: (ዛሬ ልደቷ ነው)
+*" አቡነ ተክለ አልፋ "*+
=>በ14ኛው መቶ ክ/ዘመን በኢትዮዽያ የተነሱ::
*ደብረ ድማሕን / ዲማን (ጎጃም) የመሠረቱ::
*በፍጹም ተጋድሎ የኖሩ::
*ምድረ ጎጃምን በስብከተ ወንጌል ያበሩ::
*በሊቅነታቸው የተመሠከረላቸው::
*መልክአ ኢየሱስን እንደ ደረሱ የሚነገርላቸው::
*ብዙ ተአምራትን የሠሩ (ዛሬም ድረስ የሚሠሩ)::
*የሃገራችን ትምክህት የሆኑ ታላቅ ሐዋርያዊ አባት ናቸው:: (ዛሬ ዕረፍታቸው ነው)
+*" ቅዱስ ገብረ ማርያም "*+
=>በ16ኛው መቶ ክ/ዘ በምድረ ኢትዮዽያ የተወለደ::
*ስም አጠራሩ ያማረ:
*ዛሬ እናንተና እኔ ለምናደርገው የቅዱሳን መታሰቢያ መሠረት የጣለ
*በዓመቱ የሚከበሩ ሁሉን ቅዱሳን የሚዘክር
*365ቱን ቀናት በምጽዋት የተጠመደ:
*የነዳያን አባት የሆነ:
*በአፄ ልብነ ድንግል ግራኝ አህመድ መምጣቱን ሲሰማ ያልደነገጠ:
*ሃብት ንብረቱን ለነዳያን አካፍሎ: ነጭ ልብስ ለብሶ ገዳዮቹን የጠበቀ::
*እንዲያ እንዳማረበት የግራኝ ወታደሮች የሰየፉትና ሞገስ የሆነን አባት ነው:: (ዛሬ ዕረፍቱ ነው)
በበመምህር ናሁ ሠናይ
https://youtu.be/lPNqhKdzvuw?si=yQUJ-dVhO8F92Adb
Photo unavailableShow in Telegram
✝እንኳን አደረሳችሁ !
☞ወርኀ ታኅሣሥ ቡሩክ።
ወአመ ፯፦
✝ጾመ ስብከተ ጌና፥ ዘነቢያት ወዘአበው ቀደምት ቅዱሳን (ወይእቲ ጾመ አዳም)
✝በዓል ዐቢይ ወክቡር፦ ስብከቱ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኀኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ዘሎቱ ስብሐት ወአኮቴት፥ በአፈ ነቢያት ቅዱሳን፥ ዘከመ ይትወለድ እማርያም እምቅድስት ድንግል (ስብከተ ነቢያት)
✝ተዝካረ በዓለ ሥሉስ ቅዱስ፥ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ (ገባሬ ኲሉ)
✝ወተዝካረ በዓሎሙ ለቅዱሳን፦ አባ ጊዮርጊስ ወአባ ሲኖዳ፥ አባ ባውላ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ፥ አግናጥዮስ ሐዋርያ ወአበስኪሮን መዋዒ፥ ወያዕቆብ ዘስሩግ
❖ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦
✝ክቡራን ወዐቢያን፥ ነቢያት ወአበው ቀደምት (፲ወ፭ቱ አበው፥ ፬ቱ ዐበይት፥ ፲ወ፪ቱ ደቂቅ፥ ወካልአን)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ አባ ዳንኤል ጻድቅ አበ ምኔት፥ መነኮስ ኃያል ወመስተጋድል፥ ዘአንደየ ርዕሶ በእንተ ክርስቶስ፥ ወዘጸሐፈ ገድሎሙ ለገዳማውያን (ዘደብረ ሲሐት)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ ወመስተጋድል፥ አባ ማቴዎስ ነዳይ፥ ጻድቅ ሊቀ ምኔት ዘእምርት ደብረ እስዋን፥ ዘገብረ መንክራተ፥ ወሰደደ አጋንንተ
✿አባ ሰራብዮን፥ ወአባ ኅድራ (አርዳኢሁ)
✝አብ ዐቢይ ወክቡር፥ አባ ዘካርያስ ጻድቅ፥ ብእሲ ትሩፍ ኢትዮጵያዊ (ዘፈጸመ ገድሎ በደብረ ገሊላ/ጣና)
✿ቅድስት ገዳሙ፥ ወቅዱሳን ውሉዱ መነኮሳት (እለ ፊልሞና ወእስጢፋኖስ)
✝ዐቢይ ወክቡር፥ ማር ዳንኤል ጻድቅ፥ ኢትዮጵያዊ መምህር (ዘእምአድባራተ ጎጃም)
✝ቅድስት ወቡርክት፥ ዲዮጥርስ ብጽዕት
❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡
https://t.me/zikirekdusn
Photo unavailableShow in Telegram
🕊እንኳን አደረሳችኹ ወርኃ ታኅሣሥን በሰላም ያስፈጽመን የንስሐ ልብ ይሰጠን::
🕊"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::" /ማቴ ፫:፫/
ለ ፳፻፲፰የቤት ሥራ የሚሆኑ ፯መልእክቶች
፩,እንጸልይ::
፪,አፋችንን እጃችንን እግራችንን እንሰብስበው::
፫, ከቆሻሻ ኢንተርኔት ራሳችሁን አርቁ። የምትከታተሉትን ምረጡ!
፬,ምጽዋት እንስጥ።
፭,ንሰሐ እንግባ።
፮,እንዘን እናልቅስ።
፯, ለሁሉም ነገር እንዘጋጅ
💥ስለ ንስሐ💥
✝ከቅዱስ ሙሴ ጸሊም የምንማራቸው 7 ነገሮች።
፩, 🌿ቅዱስ አብርሃምን መምሰል( ፈጣሪውን ተመራምሮ አገኘ)::
፪, 🌿ዓለምንና የዓለምን ነገሮች መታው።
፫, 🌿የንስሐ ሕይወት( ንስሐን በትጋት መፈጸም)።
፬, 🌿መታዘዝ (የሚታዘዘውን ሳያጓድል መስራትን)።
፭, 🌿ለሌሎች መኖርን።
፮, 🌿በሰው አለመፍረድን።
፯, 🌿ትሕትናን።
1,💥ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡
2,💥ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡
3, 💥በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡
4,💥የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው
4 ነገሮችን በደንብ ልብ እንበል!
1, ✨አላማ
2 ,✨እምነት
3,✨ጥረት
4 ✨ጥንቃቄ
9ኙ የቅድስና መንገዶች
፩💥ሃይማኖት
፪💥ጾም
፫💥ጸሎት
፬💥ስግደት
፭💥ምጽዋት
፮💥ፍቅር
፯💥ትህትና
፰💥ትዕግስት
፱💥የዋህነት
✨እነዚኽን ያዟቸው ተጠቀሙባቸው
እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።
✝ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት
ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን!
(የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🔗https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
One day, when the heresy was about to be read by the order of the Emperor, because the Saint removed it from the soldier’s hand and ripped it, he was beaten by the adherents (soldiers).✞The righteous Abba Daniel also at one time saw a poor man called Eulogius receiving guests [with the money he earned] after he worked as a stonecutter [the whole day]. Thus, the Saint [seeing that] delved into the Creator’s providence and asked, “O Lord! Why did You make this man poor?”
✞Then, the Lord as usual appeared to him (as He used to appear to the Saint frequently) and said, “Will you vouch for him with your soul?” And because the Saint replied, “Yes My Lord!”, our Lord gave Eulogius wealth. However, immediately after that, he became a military leader and a cruel person.
✞When the Saint heard the news; he went to see him and was beaten by Eulogius’ soldiers. Then, our Lord brought forth Abba Daniel to His throne and [wrathfully] stated, “Give me back my beloved.” But, the Mother of Light came and kissed the feet of her Son.
✞And she beseeched Him saying, “Forgive my Son!” And the Lord answered, “I will [for your sake]”. And He returned the Saint to his cell and Eulogius to his former deed. The wonders of Abba Daniel are numerous.
✞At another time, a thief entered a convent looking like Abba Daniel to steal. And the nuns thinking that it was the Saint, washed his feet and with the water wiped a blind sister and she gained her sight. And the thief shocked, repented. Abba Daniel finished his fight and passed away on this day.
✞✞✞Abba Matthew the Ascetic✞✞✞
=>The Saint was one of the spiritual children of the Great Abba Pachomius and was one of those that were called as the Stars of the Desert. He was a father that bore many disciples, lived with majestic beasts, performed many miracles and was a counselor to the grieved. Today is [the commemoration of] the day of his departure.
✞✞✞May the blessings of our Fathers indwell in us.
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 7th of Tahisas
1. Sebkete Nebiat – Ministry of the Prophets
2. Abba Daniel the Ascetic
3. Abba Matthew the Ascetic
4. Blessed Diyonteres (Diontyras)
✞✞✞ Monthly Feasts
1. The Holy Trinity (The Father, the Son and the Holy Spirit)
2. Abba Giorgis of Gascha
3. Abba Shenouda (Shenoute) (The Archimandrite)
4. Abba Daniel of the Monastery of Scete
5. Abba Paula the Monastic
6. St. Athanasius the Apostolic
7. St. Ignatius of Antioch (martyred by being given to lions)
✞✞✞“Knowing this first, that no prophecy of the scripture is of any private interpretation. For the prophecy came not in old time by the will of man: but holy men of God spake as they were moved by the Holy Ghost.”✞✞✞
2 Pet. 1:20-21
✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞
(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
=> The 15 Prophetic Fathers are
*St. Adam our father
*Seth
*Enos
*Cainan
*Mahalaleel
*Jared
*Enoch
*Methuselah
*Lamech
*Noah
*Abraham
*Isaac
*Jacob
*Moses and
*Samuel.
=>The 4 Major Prophets are
*St. Isaiah (Of Eminent Word)
*St. Jeremiah
*St. Ezekiel and
*St. Daniel.
=>The 12 Minor Prophets are
*St. Hosea
*Amos
*Micah
*Jonah
*Nahum
*Obadiah
*Zephaniah
*Haggai
*Joel
*Habakkuk
*Zechariah and
*Malachi.
=>Those called Other Prophets include
*Joshua
*Samson
*Jephthah
*Gideon
*David
*Solomon
*Elijah
*Elisha … and others.
=>Prophets are also divided by their cities and called as
* Of Judea/Judah (Jerusalem)
* Of Samaria (Israel) and
* Of Babylon (During exile)
=>And according to divisions by time, they are divided as
*From Adam up to Joseph (Prophets of the Era of the Fathers/Patriarchs)
*From Arch-prophet Moses up to Prophet Samuel (Prophets of the Era of Judges)
*From St. David up to Zerubbabel (Prophets of the Era of Kings)
*And the prophets after the death of Zerubbabel up to John the Baptist are called Prophets of the Era of Priests.
✞✞✞Abba Daniel the Great✞✞✞
=>The invocation of the name of this Holy Father is glorious as he was a holy light to the monks and has seen the tang of the Heavenly Kingdom in what was an ample life of purity. Abba Daniel was an Egyptian who entered a monastery in his youth shunning the world.
✞The time [during which he lived] was the Era of the Righteous (the 5th Century). He was known in the Monasteries of Scetes – of St. Macarius and Sheahat. The great abode of the Saints, the Monastery of Sheahat, is still called by his name. And the reason for this is because he spent many years there in the spiritual fight and bore spiritual fruits and disciples in holiness.
✞So, he is to this day called Abba Daniel of the Monastery of Sheahat. He is also known as, “of the Monastery of Scetes”. The Monastery of Scetes is the legacy of the Great St. Macarius and it takes the first place from the [monasteries of the] world for the area it occupies and for bringing forth numerous saints.
✞The fathers that were appointed to be abbots of the monastery were always those that had reached perfection and their honor is above a Patriarch. Abba Daniel, after many years of sanctity, was appointed as the abbot of the monastery and led numerous monks to righteousness.
✞The Saint did not have time to eat or sleep because of his diligence. During the day, he absolved the sins of the monks (listened to confessions), healed the sick and oversaw the workings of the monastery. And when it became night time, he went out to the desert where the sowah (the spirit-borne anchorites) dwelt.
✞There, he used to spend the night wandering in the desert looking for the spirit-borne fathers. And because of this, he has written the acts of many sowah/anchorites. And when they passed away, he has participated in shrouding and burying them. And he has done a great deed.
✞From those Saints that he shrouded, buried and wrote accounts of, St. Amete Kirstos (Christodoula) the Israelite (that lived for 38 years naked in the wilderness) and St. Patricia (St. Anastasia the Patrician) the Queen (one who left her throne and lived in hiding) can be mentioned.
✞Beyond that, Abba Daniel knew how to show the honor of those that were loathed by people. For example, St. Anasima, who was thought to have been a mad woman and was left on the gate of a nunnery; and St. Meherka (Mark), who was also thought to have been a mad man and about whom even the Archbishop of Alexandria did say, “He is insane”; the Saint showed that they were both saints who had hidden themselves [as fools for Christ].
✞Abba Daniel was also an apostolic because he used to give diligent answers to the Chalcedonian heresy that spread during that time from a heretical letter called “The Tome of Leo” which was in circulation.
Memhir Esuendale:
#Feasts of #Tahisas_7
✞✞✞On this day we start the liturgical week/season honoring the Ministry of the Prophets (Sebkete Nebiyat – Tidings of the Prophets) and commemorate the Saints Abba Daniel and Abba Matthew✞✞✞
✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞
✞✞✞Sebket – Tiding✞✞✞
=>This day is called “Sebket - Tidings” according to the Tradition of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. “Sebket” by itself means “Good tidings or announcing of a glad news” but the main mystery behind the term is associated with soteriology (the teaching about salvation).
✞On this day (week) all the prophets and their prophecies are remembered. And the Season of Sebket/Tidings falls from Tahisas 7 – 13 (December 16 - 22). And if asked “How did that came to be?”, it was as follows.
✞When God placed Adam in paradise after endowing him with 7 gifts, he ate the fruit that he was told not to. And for this, he was separated from his Creator, and was subjected to the death of the soul upon the death of the flesh and to going to Gehenna upon being buried. However, later on, because he repented, God gave him a covenant saying, “I will save you after 5 and a half days, being born from your descendants”.
✞After that, for 5,500 years, time started to be counted in descending order. Hence, prophecies started to be told, jubilees began to be counted and typologies were made about the incarnation of God and Him becoming man and saving the world.
✞From the time of Adam to Moses (Era of the Fathers/Patriarch) typologies were numerous. Then, from Moses to David (Era of the Judges) the typologies became pronounced. And from St. David, the one after God’s own heart, to St. Malachi (Era of the Prophets/Kings) prophecies about Christ and about His mother who was His abode flowed like a torrent.
✞Prophets waiting for the coming of the Messiah lived in fasts, prayers and austerity. They wept and it reached before God and the Savior, Christ, was born and saved them.
✞A prophet is a person who knows the past (what has happened previously and had remained a mystery) and the future (what will happen). The gift of prophecy is God’s by nature [since He is omniscient] and He gives it to the one He loves by grace. And these fathers and mothers who were endowed with the gift of prophecy were called “Holy Prophets.”
✞Even though, the Era of the Prophets was in the Old Testament, the gift is given until the Second Coming to those that God wills to give. Amongst the Apostles, there were prophets like St. Agabus as well (Acts 11.28).
✞The Holy Prophets sent by God, counsel people to reconcile with God. And they also rebuke. Because of their true faith and purity, they have seen God in different representations and manifestations.
As it is said by Abba Heryacos (Cyriacus), “…the prophets saw the Lord through the purity of the spirit seeing Him face to face” (Anaphora of St. Mary no. 161).
✞The end of most prophets was by receiving tribulation. Because they spoke the truth, some were tried with fire some with the sword and some with the saw. And the others were thrown to lions and the rest stoned.
✞And for their suffering, they are called as the foundations of the Church. And our Lord has said to His disciples about the trials of the prophets, “other men laboured, and ye are entered into their labours” (John 4:38).
✞The prophets have tried and wanted to see our Lord Jesus Christ and His Virgin Mother. As the Lord had said in the Gospel, “many prophets and righteous men have desired to see those things which ye see” (Matt. 13.17/ 1Pet. 1.10). Nonetheless, now, they rejoice in heaven, having much grace and given honor.
✞The holy prophets mainly are divided into four as follows:
*The 15 prophetic fathers
*The 4 major prophets
*The 12 minor prophets and
*Other prophets
<< ❇️ታላቁ አባ ዳንኤል ❇️>>
ይህ ቅዱስ አባት ስም አጠራሩ ክቡር ነው:: በሁሉ ነገሩ የተቀደሰ የገዳማውያን መብራትም ነው:: ከተረፈ ንጹሕ ሕይወቱ ጣዕመ መንግስተ ሰማያትን አይቷልና:: አባ ዳንኤል በትውልድ ግብጻዊ ሲሆን ዓለምን ንቆ (መንኖ) ገዳም የገባው ገና በወጣትነቱ ነው::
ጊዜውም ዘመነ ጻድቃን (በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን) ነበር:: በገዳመ አስቄጥስና በደብረ ሲሐት ይታወቃል:: ታላቁዋ መካነ ቅዱሳን ገዳመ ሲሐት ዛሬም ድረስ በስሙ የምትጠራ ሲሆን ለዚህም ምክንያቱ እጅግ ለብዙ ዘመናት በውስጧ ተጋድሎ ፍሬ ስላፈራባት: ደቀ መዛሙርትን በቅድስና ስለ ወለደባት ነው::
ስለዚህም ዛሬም ድረስ "አባ ዳንኤል ዘደብረ ሲሐት" ተብሎ ሲጠራ ይኖራል:: ሌላኛው ስሙ ደግሞ "ዘገዳመ አስቄጥስ" ይሰኛል:: ገዳመ አስቄጥስ የታላቁ ቅዱስ መቃርስ ርስት ሲሆን በዓለም በስፋትም: ብዙ ቅዱሳንን በማፍራትም አንደኛ የሆነ ገዳም ነው::
በዚህ ገዳም ላይ አበ ምኔት ሁነው የሚሾሙ አበው ሁሌም የብቃት መዓርግ ላይ የደረሱ ሲሆኑ ክብራቸው ከፓትርያርክ በላይ ነው:: አባ ዳንኤልም ከብዙ የቅድስና ዓመታት በሁዋላ በአስቄጥስ ገዳም አበ ምኔት ሆኖ ተሹሞ እልፍ አእላፍ መነኮሳትን በጽድቅ መንገድ መርቷል::
ቅዱሱ ከትጋቱ የተነሳ ለምግብና ለእንቅልፍ ጊዜ አልነበረውም:: ቀን ቀን መነኮሳቱን ሲናዝዝ: ድውያንን ሲፈውስ: ሥርዓተ ገዳምን ሲቆጣጠር ይውላል:: ልክ ሲመሽ ጭው ወዳለውና ስውራን ወደ ሚገኙበት በርሃ ይወጣል::
በዚያም ሙሉውን ሌሊት የተሰወሩ አባቶችን ሲፈልግ ያድር ነበር:: በዚህም ምክንያት የብዙ ስውራንን ገድል የጻፈ ሲሆን ባረፉ ጊዜም ገንዞ በመቅበር በረከታቸውን ተሳትፏል:: ታላቅ ሙያንም ፈጽሟል::
እርሱ ገንዞ ቀብሮ: ዜናቸውን ከጻፈላቸው ሥውራን ቅዱሳንም እንደ አብነት እሥራኤላዊቷን ቅድስት ዓመተ ክርስቶስን (ለ38 ዓመት ራቁቷን በሥውር የኖረች) እና ቅድስት በጥሪቃ ንግሥትን (መንግስቷን ትታ በሥውር የኖረች ናት) መጥቀስ እንችላለን::
ከዚህ ባለፈም አባ ዳንኤል በሰው ዘንድ የተናቁትንም ማክበርን ያውቅበታል:: ለምሳሌ በሴቶች ገዳም "እብድ" ናት ተብላ በበር የተጣለችውን ቅድስት አናሲማን: በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ዻዻሳቱ ሳይቀር "እብድ" ነው ብለው የናቁትን ቅዱስ ምሕርካን: እብድ ሳይሆኑ ራሳቸውን የሠወሩ ቅዱሳን መሆናቸውን ገልጧል::
አባ ዳንኤል ሐዋርያዊም ነበር:: በጊዜው ጦማረ ልዮን የሚባል የኑፋቄ ደብዳቤ ይላክ ነበርና ለዚህ ኬልቄዶናዊ ኑፋቄ በትጋት ምላሽ ይሰጥ ነበር:: አንድ ቀንም በንጉሥ ትዕዛዝ ኑፋቄው በእርሱ ገዳም ሊነበብ ሲል ቅዱሱ ከወታደሩ ቀምቶ ስለ ቀደደው ለሞት እስኪደርስ ደብድበውታል::
ጻድቁ አባ ዳንኤል አንዴ አውሎጊስ የሚባል ደሃ ድንጋይ ጠርቦ እንግዳ ሲቀበል ተመልክቶ "ጌታ ሆይ! ይህንን ደግ ሰው ለምን ደሃ አደረከው?" ሲል በፈጣሪ ሥራ ገባ::
ጌታም እንደ ወትሮው በገሃድ ተገልጦ "በነፍስህ ትዋሰዋለህ?" አለው:: "አዎ ጌታየ" ስላለው ጌታችን ለአውሎጊስ ሃብትን ሰጠው:: ግን ወዲያው የጦር አለቃና ጨካኝ ሰው ሆነ::
ጻድቁ ወሬውን ሰምቶ ሊጠይቅ ቢሔድ የአውሎጊስ ወታደሮች ደበደቡት:: ጌታችንም አባ ዳንኤልን ወደ ፍርድ ዙፋኑ አቅርቦ "ወዳጄን መልስልኝ" አለው:: እመ ብርሃን ግን ቀርባ የልጇን እግር ሳመች::
"ልጄ ሆይ ማር!" አለችው:: ጌታም "እሺ" ብሎ ጻድቁን ወደ በአቱ: አውሎጊስን ወደ ቀደመ ግብሩ መለሳቸው:: የአባ ዳንኤል ድንቁ ብዙ ነው::
ሌላው ቢቀር ሽፍታ አባ ዳንኤልን መስሎ ወደ ደናግል ገዳም: ሊዘርፍ: በማታለል ገባ:: ደናግሉም ጻድቁ መስሏቸው እግሩን አጥበው ዐይነ ስውሯን ቢቀቧት ዐይኗ በርቷል:: ሽፍታውም ደንግጦ ንስሃ ገብቷል:: አባ ዳንኤል ግን ተጋድሎውን ፈጽሞ በዚህች ቀን ዐርፏል::
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn
ከዚህ ባለፈም አባ ዳንኤል በሰው ዘንድ የተናቁትንም ማክበርን ያውቅበታል:: ለምሳሌ በሴቶች ገዳም "እብድ" ናት ተብላ በበር የተጣለችውን ቅድስት አናሲማን: በእስክንድርያ ከተማ ሊቀ ዻዻሳቱ ሳይቀር "እብድ" ነው ብለው የናቁትን ቅዱስ ምሕርካን: እብድ ሳይሆኑ ራሳቸውን የሠወሩ ቅዱሳን መሆናቸውን ገልጧል::አባ ዳንኤል ሐዋርያዊም ነበር:: በጊዜው ጦማረ ልዮን የሚባል የኑፋቄ ደብዳቤ ይላክ ነበርና ለዚህ ኬልቄዶናዊ ኑፋቄ በትጋት ምላሽ ይሰጥ ነበር:: አንድ ቀንም በንጉሥ ትዕዛዝ ኑፋቄው በእርሱ ገዳም ሊነበብ ሲል ቅዱሱ ከወታደሩ ቀምቶ ስለ ቀደደው ለሞት እስኪደርስ ደብድበውታል::
ጻድቁ አባ ዳንኤል አንዴ አውሎጊስ የሚባል ደሃ ድንጋይ ጠርቦ እንግዳ ሲቀበል ተመልክቶ "ጌታ ሆይ! ይህንን ደግ ሰው ለምን ደሃ አደረከው?" ሲል በፈጣሪ ሥራ ገባ::
ጌታም እንደ ወትሮው በገሃድ ተገልጦ "በነፍስህ ትዋሰዋለህ?" አለው:: "አዎ ጌታየ" ስላለው ጌታችን ለአውሎጊስ ሃብትን ሰጠው:: ግን ወዲያው የጦር አለቃና ጨካኝ ሰው ሆነ::
ጻድቁ ወሬውን ሰምቶ ሊጠይቅ ቢሔድ የአውሎጊስ ወታደሮች ደበደቡት:: ጌታችንም አባ ዳንኤልን ወደ ፍርድ ዙፋኑ አቅርቦ "ወዳጄን መልስልኝ" አለው:: እመ ብርሃን ግን ቀርባ የልጇን እግር ሳመች::
"ልጄ ሆይ ማር!" አለችው:: ጌታም "እሺ" ብሎ ጻድቁን ወደ በአቱ: አውሎጊስን ወደ ቀደመ ግብሩ መለሳቸው:: የአባ ዳንኤል ድንቁ ብዙ ነው::
ሌላው ቢቀር ሽፍታ አባ ዳንኤልን መስሎ ወደ ደናግል ገዳም: ሊዘርፍ: በማታለል ገባ:: ደናግሉም ጻድቁ መስሏቸው እግሩን አጥበው ዐይነ ስውሯን ቢቀቧት ዐይኗ በርቷል:: ሽፍታውም ደንግጦ ንስሃ ገብቷል:: አባ ዳንኤል ግን ተጋድሎውን ፈጽሞ በዚህች ቀን ዐርፏል::
<< አባ ማቴዎስ ገዳማዊ >>
ጻድቁ ከታላቁ ቅዱስ ዻኩሚስ የመንፈስ ልጆች አንዱ ሲሆን የበርሃ ኮከቦች ከሚባሉት አንዱ ነው:: ብዙ ደቀ መዛሙርትን ያፈራ: ከግሩማን አራዊት ጋር የኖረ: ብዙ ተአምራትን የሠራ: ናዛዜ ሕዙናን የሆነ አባት ነው:: ዛሬ ዕረፍቱ ነው::
የአባቶቻችን በረከት ይደርብን::
=>ታሕሳስ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ስብከተ ነቢያት
2.አባ ዳንኤል ገዳማዊ
3.አባ ማቴዎስ ገዳማዊ
4.ብጽዕት ዲዮጥርስ
=>ወርሐዊ በዓላት
1.ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)
2.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
3.አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን አለቃ)
4.አባ ባውላ ገዳማዊ
5.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
6.ቅዱስ አግናጥዮስ (ለአንበሳ የተሰጠ)
"ይህን በመጀመሪያ እወቁ:: በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም:: ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና:: ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ::"
(2ዼጥ. 1:20)
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>
"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn
††† እንኳን ለስብከተ ነቢያት እና ለአበው ጻድቃን አባ ዳንኤል ወአባ ማቴዎስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††
††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††
<<< ❇️ስብከት ❇️>>>
ይህች ዕለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት "ስብከት" ትባላለች:: ስብከት ማለት በቁሙ "የምስራች: አዲስ ዜና መንገርን" የሚመለከት ሲሆን ዋናው ምሥጢር ግን ከነገረ ድኅነት (ከመዳን ትምሕርት) ጋር የተገናኘ ነው::
በዚህ ዕለት (ሳምንት) ሁሉም ነቢያት ከነ ትንቢታቸው ይታሰባሉ:: ዘመነ ስብከትም ከታሕሳስ 7 እስከ 13 ያለውን ይይዛል:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
እግዚአብሔር አዳምን በ7 ሃብታት አክብሮ በገነት ቢያኖረው "አትብላ" የተባለውን ዕፀ በለስ በላ:: በዚህም ከፈጣሪው ተጣልቶ: በሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ: በርደተ መቃብር ርደተ ገሃነም ተፈረደበት:: በሁዋላ ግን ንስሃ ስለ ገባ "ከ5 ቀን ተኩል (5,500 ዘመን) በሁዋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ቃል ኪዳንን ሰጠው::
ከዚህ በሁዋላ ለ5,500 ዘመናት ጊዜ ወደ ታች ይቆጠር ጀመር:: ስለ እግዚአብሔር ሰው መሆንና ዓለምን ማዳንም ትንቢት ይነገር: ሱባኤ ይቆጠር: ምሳሌም ይመሰል ገባ::
ከአዳም እስከ ሙሴ (ዘመነ አበው) ምሳሌያት ይበዛሉ:: ከሙሴ እስከ ዳዊት (ዘመነ መሣፍንት) ምሳሌያቱ እየጐሉ መጥተዋል:: ከልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እስከ ቅዱስ ሚልክያስ ድረስ (በዘመነ ነቢያት/ነገሥት) ግን ትንቢቶች ስለ ክርስቶስና ስለ ማደሪያ እናቱ እንደ ጐርፍ ፈሰዋል::
ነቢያትም የመሲህን መምጣት እየጠበቁ በጾም: በጸሎትና በትሕርምት ኑረዋል:: እንባቸውንም አፍሰው ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶላቸዋል:: መድኅን ክርስቶስም ተወልዶ አድኗቸዋል::
ነቢይ ማለት በቁሙ ኃላፍያትን (አልፎ የተሠወረውን ምሥጢር): መጻዕያትን (ለወደ ፊት የሚሆነውን) የሚያውቅ ሰው ማለት ነው:: ሃብተ ትንቢት የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ሲሆን እርሱ ለወደደው በጸጋ ይሰጠዋል:: እነዚህም ከጌታ ሃብተ ትንቢት የተሰጣቸው አባቶችና እናቶች "ቅዱሳን ነቢያት" በመባል ይታወቃሉ::
ዘመነ ነቢያት ተብሎ የሚታወቀው ብሉይ ኪዳን ቢሆንም እስከ ምጽዓት ድረስ ጸጋውን እግዚአብሔር ለፈቀደላቸው አይነሳቸውም:: በሐዋርያት መካከልም ቅዱስ አጋቦስን የመሰሉ ነቢያት ነበሩ:: (ሐዋ. 11:27) ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር እየተላኩ ሰውን ከፈጣሪው እንዲታረቅ ይመክራሉ: ይገስጻሉ::
ከበጐ ሃይማኖታቸውና ንጽሕናቸው የተነሳም እግዚአብሔርን በተለያየ አርአያና አምሳል አይተውታል::
"እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር: ወተናጸሩ ገጸ በገጽ" እንዳለ አባ ሕርያቆስ:: (ቅዳሴ ማርያም)
የብዙ ነቢያት ፍጻሜአቸው መከራን መቀበል ነው:: እውነትን ስለ ተናገሩ: አንዳንዶቹም በእሳት: አንዳንዶቹም በሰይፍ: አንዳንዶቹም በመጋዝ ተፈትነዋል:: ሌሎቹ ለአናብስት ሲጣሉ ቀሪዎቹ ደግሞ በድንጋይ ተወግረዋል::
ስለዚህም መከራቸው ለቤተ ክርስቲያን መሠረት ተብለዋል:: ጌታም ለደቀ መዛሙርቱ "ሌሎች ደከሙ: እናንተ በድካማቸው ገባችሁ" ብሎ የነቢያቱን መከራ ተናግሯል:: (ዮሐ. 4:36)
ነቢያት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እና ድንግል እናቱን ለማየት ብዙ ጥረዋል: ሽተዋልም:: "ብዙ ነቢያትና ጻድቃን እናንተ የምታዩትን ሊያዩ ሹ" እንዳለ ጌታ በወንጌል:: (ማቴ. 13:16, 1ዼጥ. 1:10) ዛሬ ግን በሰማያት ጸጋ በዝቶላቸው: ክብር ተሰጥቷቸው ሐሴትን ያደርጋሉ::
ቅዱሳን ነቢያት በዋነኝነት 15ቱ አበው ነቢያት: 4ቱ ዐበይት ነቢያት: 12ቱ ደቂቀ ነቢያትና ካልአን ነቢያት ተብለው በ4 ይከፈላሉ::
"15ቱ አበው ነቢያት" ማለት:-
*ቅዱስ አዳም አባታችን
*ሴት
*ሔኖስ
*ቃይናን
*መላልኤል
*ያሬድ
*ኄኖክ
*ማቱሳላ
*ላሜሕ
*ኖኅ
*አብርሃም
*ይስሐቅ
*ያዕቆብ
*ሙሴና
*ሳሙኤል ናቸው::
"4ቱ ዐበይት ነቢያት"
*ቅዱስ ኢሳይያስ ልዑለ ቃል
*ቅዱስ ኤርምያስ
*ቅዱስ ሕዝቅኤልና
*ቅዱስ ዳንኤል ናቸው::
"12ቱ ደቂቀ ነቢያት"
*ቅዱስ ሆሴዕ
*አሞጽ
*ሚክያስ
*ዮናስ
*ናሆም
*አብድዩ
*ሶፎንያስ
*ሐጌ
*ኢዩኤል
*ዕንባቆም
*ዘካርያስና
*ሚልክያስ ናቸው::
"ካልአን ነቢያት" ደግሞ:-
*ኢያሱ
*ሶምሶን
*ዮፍታሔ
*ጌዴዎን
*ዳዊት
*ሰሎሞን
*ኤልያስና
*ኤልሳዕ ሌሎችም ናቸው::
ነቢያት በከተማም ይከፈላሉ::
*የይሁዳ (ኢየሩሳሌም):
*የሰማርያ (እሥራኤል)ና
*የባቢሎን (በምርኮ ጊዜ) ተብለው ይጠራሉ::
በዘመን አከፋፈል ደግሞ:-
*ከአዳም እስከ ዮሴፍ (የዘመነ አበው ነቢያት):
*ከሊቀ ነቢያት ሙሴ እስከ ነቢዩ ሳሙኤል (የዘመነ መሳፍንት ነቢያት)
*ከቅዱስ ዳዊት እስከ ዘሩባቤል ያሉት (የዘመነ ነገሥት ነቢያት):
*ከዘሩባቤል ዕረፍት እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ያሉት ደግሞ (የዘመነ ካህናት ነቢያት) ይባላሉ::
<< ታላቁ አባ ዳንኤል >>
ይህ ቅዱስ አባት ስም አጠራሩ ክቡር ነው:: በሁሉ ነገሩ የተቀደሰ የገዳማውያን መብራትም ነው:: ከተረፈ ንጹሕ ሕይወቱ ጣዕመ መንግስተ ሰማያትን አይቷልና:: አባ ዳንኤል በትውልድ ግብጻዊ ሲሆን ዓለምን ንቆ (መንኖ) ገዳም የገባው ገና በወጣትነቱ ነው::
ጊዜውም ዘመነ ጻድቃን (በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን) ነበር:: በገዳመ አስቄጥስና በደብረ ሲሐት ይታወቃል:: ታላቁዋ መካነ ቅዱሳን ገዳመ ሲሐት ዛሬም ድረስ በስሙ የምትጠራ ሲሆን ለዚህም ምክንያቱ እጅግ ለብዙ ዘመናት በውስጧ ተጋድሎ ፍሬ ስላፈራባት: ደቀ መዛሙርትን በቅድስና ስለ ወለደባት ነው::
ስለዚህም ዛሬም ድረስ "አባ ዳንኤል ዘደብረ ሲሐት" ተብሎ ሲጠራ ይኖራል:: ሌላኛው ስሙ ደግሞ "ዘገዳመ አስቄጥስ" ይሰኛል:: ገዳመ አስቄጥስ የታላቁ ቅዱስ መቃርስ ርስት ሲሆን በዓለም በስፋትም: ብዙ ቅዱሳንን በማፍራትም አንደኛ የሆነ ገዳም ነው::
በዚህ ገዳም ላይ አበ ምኔት ሁነው የሚሾሙ አበው ሁሌም የብቃት መዓርግ ላይ የደረሱ ሲሆኑ ክብራቸው ከፓትርያርክ በላይ ነው:: አባ ዳንኤልም ከብዙ የቅድስና ዓመታት በሁዋላ በአስቄጥስ ገዳም አበ ምኔት ሆኖ ተሹሞ እልፍ አእላፍ መነኮሳትን በጽድቅ መንገድ መርቷል::
ቅዱሱ ከትጋቱ የተነሳ ለምግብና ለእንቅልፍ ጊዜ አልነበረውም:: ቀን ቀን መነኮሳቱን ሲናዝዝ: ድውያንን ሲፈውስ: ሥርዓተ ገዳምን ሲቆጣጠር ይውላል:: ልክ ሲመሽ ጭው ወዳለውና ስውራን ወደ ሚገኙበት በርሃ ይወጣል::
በዚያም ሙሉውን ሌሊት የተሰወሩ አባቶችን ሲፈልግ ያድር ነበር:: በዚህም ምክንያት የብዙ ስውራንን ገድል የጻፈ ሲሆን ባረፉ ጊዜም ገንዞ በመቅበር በረከታቸውን ተሳትፏል:: ታላቅ ሙያንም ፈጽሟል::
እርሱ ገንዞ ቀብሮ: ዜናቸውን ከጻፈላቸው ሥውራን ቅዱሳንም እንደ አብነት እሥራኤላዊቷን ቅድስት ዓመተ ክርስቶስን (ለ38 ዓመት ራቁቷን በሥውር የኖረች) እና ቅድስት በጥሪቃ ንግሥትን (መንግስቷን ትታ በሥውር የኖረች ናት) መጥቀስ እንችላለን::
✞Finally, it settled in a different location. And on that day by the intercession of the Virgin and the prayers of the Saints a great majesty befell. However, St. Simeon immediately disappeared as he despised vainglory. And Abba Abraham labored the rest of his life and departed. Today is the commemoration of both [fathers].
✞✞✞The scholars admiring St. Simeon thus say;
“Salutations to Saint Simeon who was revealed by Mary’s word
Who blinded his eye for the sake of her Son’s command
So they will not notice him or give him merit
He prayed standing behind the Prelate
And removed a Mount and sited a Mount.”
(Arke)
✞✞✞May the God of the Saints not deprive us of the faith they used to remove a mountain with. And may He grant us from their blessings.
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 6th of Tahisas
1. St. Arsema the Virgin (Hripsime)
2. “119” Martyrs, her followers
3. St. Simeon the Righteous (the Cobbler)
4. Abba Abraham the Syrian, 62nd Patriarch of Alexandria
5. St. Anatolius the Martyr
✞✞✞ Monthly Feasts
1. Holy Debre Quosquam
2. Our Father Adam and our Mother Eve
3. Our Father Noah and our Mother Haikel
4. St. Elijah Prophet
5. St. Basil of Caesarea
6. St. Joseph the Carpenter
7. St. Salome
8. Abba Arke Selus
9. Abba Tsige Dingel
✞✞✞“. . . for verily I say unto you, If ye have faith as a grain of mustard seed, ye shall say unto this mountain, Remove hence to yonder place; and it shall remove; and nothing shall be impossible unto you.”✞✞✞
Matt. 17:20
✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞
(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
