es
Feedback
️ ንስር አማራ🦅

️ ንስር አማራ🦅

Ir al canal en Telegram

የተቀደሰን ነገር በእግሩ ለሚረግጥ ፥ተመልሶም ያጎረሰውን እጅ ለሚናከስ ርኩስ መጫወቻ የማይሆን የነቃ ማህበረሰብ እስክንፈጥር ድረስ ብዕራችን አይነጥፍም። አንድ አማራ ለሁሉም አማራ ፥ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ። 💚💛❤️ እኛን በውስጥ ለማናገር @NISIREamhra2 @NISIREamhraa_bot 👈 ይችን አድራሻ ይጠቀሙ🦅 ንስር ዐማራ🦅 #የግፉአን_ድምፅ t.me/NISIREamhra

Mostrar más
2025 año en númerossnowflakes fon
card fon
63 130
Suscriptores
-2124 horas
-2237 días
-78730 días
Archivo de publicaciones
🔥የምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጥምረት ዳውንት እና ፀሃይ መውጫ ላይ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ‼️ የምኒልክ ዕዝ አሃዶች በጥምረት ዳውንት እና ፀሃይ መውጫ ላይ ዛሬ ህዳር 23/2018 ዓ.ም ማለዳ 3:00 ጀምሮ እስከ ቀን 6:00 ከፋሽስቱ ብልፅግና አገዛዝ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ጋር በመፋለም ታላቅ ድል አስመዝግበዋል:: ጠላት ዳውንት እና ፀሃይ መውጫ ከተማን ለመቆጣጠር ከኮንና ጋሼና አንድ ክፍለጦር ዙ23ን ጨምሮ እንዲሁም ከወገል ጤና አንድ ክፍለ ጦር ዙ 23 ጋር ወደ ዳውንትና ፀሃይ መውጫ ማጥቃት ያደረገ ሲሆን ከምስራቅ አማራ ኮር 2 ዞብል አምባ ክፍለ ጦር እና ከደጋው መብረቅ ኮር ከፅናት መክትና ሰንጥቅ ክፍለ ጦር የተውጣጡ ሻለቆች እንዲሁም ሌሎች በመደራጀት ላይ ያሉ አሃዶች በጥምረት የጠላትን ሰራዊት ለጊዜው በስም ያልታወቁ አመራሮችን ጨምሮ በመደምሰስና በማቁሰል ከባድ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ በማድረስ ብሎም ቀጠናውንና ከተሞቹን በማስከበር ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል:: በዚህ በድንቅ መናበብ በተመዘገበ ታላቅ ፍልሚያና ድል የጠላት ሰራዊት በሁሉም አቅጣጫ የተመታ ሲሆን አስከሬንና ቁስለኛውንም እያነሳ ወደመጣበት አቅጣጫ ሽሽቷል:: በተጋድሎው በመደራጀት ላይ ያለ የልዩ ዘመቻ አሃድም የተሳተፈ ሲሆን ከልጅ እያሱ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር አንድ ጓድ በውጊያ መሃል ደፈጣ ጥቃት በመፈፀም ታላቅ ጀብድ ሰርተዋል:: በዚህ ታላቅ ተጋድሎ ከባድ ምት የተመታው አገዛዙ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የገባ ሲሆን የደላንታና የወገል ጤና የብልፅግና ካድሬዎችና አመራሮች ተከበናል መላም የለን እያሉ ወደ ደሴ ከተማ መሸሽ ጀምረዋል:: ውጊያው አሁንም ሌሎች አሃዶች ተጨምረውበት ተጠናክሮ ቀጥሏል:: ዝርዝር መረጃ ይዘን እንመጣለን! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ©አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 23/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
103👍 9👏 5💯 2
🔥#የዘጋርዲያን_ዘገባ‼️ ጓደኛዬ በወታደር (በመከላከያ) ስለተደፈረች ወደ ትግል ገባው ! ፋኖን ከተቀላቀሉ አንዷ! 👉የ83 አመት አዛውንት በድሮን ጥቃት ተገድለዋል 👉የ 5 አመት ህጻን ከመንግስት በተተኮሰ ከባድ መሳርያ በመገደሉ እናት ልቧ ተሰብሯል! በአማራ ክልል እየተፈጸሙ ስላሉ ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶች ፣ ስላለው ሰብአዊ ቀውስ እና የፋኖ ትግል ዙርያ ዘጋድርያን (theguardian) "Inside Ethiopia’s Fano insurgency – photo essay" በሚል ርዕስ ዛሬ ባቀረበው የፎቶ ዘገባ ጸሀፊው በወሎ አከባቢ የፋኖን የማሰልጠኛ ቦታዎች እንደጎበኘ እና ህዝብ ላይ ተፈጸመ የተባለውን ሰብአዊ መብት ጥሰት መረጃዎችን ማሰባሰቡን ገልጿል:: የአማራ ፋኖ አብዛኛውን (ወደ 80%) የሚሆነውን የአማራ ክልል በተለይም ገጠራማ አከባቢዎችን እያስተዳደርኩ እገኛለው ማለቱን ከመሪዎቹ መስማቱን ገልጿል:: ለምን የፋኖን ትግል እንደተቀላቀለች ከስልጠና ሜዳ ለዘጋቢው  የገለጸችው "ከዚህ ከ30 ኪ.ሜ በላይ ርቀት ላይ ካለ መንደር ነው የመጣሁት። እዚያም ከጓደኞቼ የ22 ዓመቷ ደርቤ በወታደሮች (በመከላከያ) አፍነው  እና ደፍረው ወደ ጎዳና ጥለዋታል። በዚያን ጊዜ መዋጋት እንዳለብኝ ወሰንኩኝ።" ማለቷን ዘግቦታል:: ሙሉ ዘገባውን ዘጋርዲያን ላይ ተመልከቱት። #Ethiopia: Widespread rights abuses in #Amhara region as federal forces move to battle Fano insurgency – the Guardian reveals Federal forces committed abuses in Amhara region, including kidnappings, massacres, sexual violence and attacks on humanitarian personnel, in an attempt to quell the Fano insurgency in Ethiopia’s Amhara region, the Guardian newspaper said in its photographic report. It added that the situation is out of control, with more than 2 million people in urgent need of humanitarian assistance in a region that is also hosting refugees from the war in Sudan. According to the Guardian newspaper in its photographic report, the Ethiopian federal army is regularly accused of massacres, arbitrary arrests, sexual violence and drone attacks targeting civilians in Amhara. Civilians interviewed described losing relatives to drone strikes and shelling, further fueling anger at the central government. The report notes that while the Fano militia initially enjoyed broad community support, worsening insecurity and economic collapse are gradually undermining this trust, with some Fano groups increasingly accused of extorting civilians, particularly at checkpoints. Once allies of the federal government during the Tigray war, the Fano turned against Addis Abeba after the Pretoria Agreement and the federal decision to dismantle regional special forces, which many Amhara fighters perceived as a direct threat to their security. Thousands of former special forces personnel subsequently joined the Fano, creating a fragmented armed movement estimated at nearly 20,000 fighters. The Guardian says the Fano now control large rural areas of Amhara, while federal forces are largely confined to major towns, and both sides hold alternating areas of control as fighting intensifies. https://www.theguardian.com/artanddesign/2025/dec/01/inside-ethiopia-fano-insurgency-photo-essay
Mostrar todo...
176👍 31💔 12😢 4
🔥#የስለጠና_ጥሪ_ማስታወቂያ ‼️ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር አዲስ ሰልጣኝ የፋኖ አባላትን ለማሰለጠን በዝግጅት ላይ ይገኛል። ሆኖም ማንኛውም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርት የምታሟሉ ስልጣኞች መሰልጠን የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። 1. ዕድሜ ከ18 አመት በላይ/የሆነች 2. ከደባል ሱስ ነፃ የሆነ/የሆነች 3. ከማንኛውም ወንጀል ነፃ የሆነ/የሆነች 4. የሚሰጠውን ማነኛውም ግዳጅ በአግባቡ መወጣት የሚችል 5. የጤና ችግር የሌለበት/የሌለባት 6. የመመዝገቢያ ቦታ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ አንደኛ ኮር በሚንቀሳቀስበት ሁሉም ቦታዎች 7. ፆታ ወንድ/ ሴት 8. የመመዝገቢያ ቀን ህዳር 22/03/2018 ዓ.ም በማንኛውም አካባቢ የምትገኙ ወጣቶች ትግላችንን በመቀላቀል መዋል ማደር ቅንጦት ሆኖበት በሰቆቃ ውስጥ ላለው የአማራ በጋራ እንቁም!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ድል ለአማራ ህዝብ ©ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ ኮር ስልጠናና ክህሎት መምሪያ #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 22/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
119👍 40🙏 11
🔥#አራት_አድማ_ብተና_ተወገዷል‼              #ቲሊሊ‼ አፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ  ክፍለ ጦር ቲሊሊ ከተማ ቦታ የያዘዉ ሆድ አደር አድማ ብተና በፊት ሲጠብቅ በጀርባው በመግባት 4ቱ በማስወገድ 5ቱ ከባድ ቁስለኛ አድርጓቸዋል። ልማደኛው 44ኛ ክፍለ ጦር በተደጋጋሚ የጠላትን አከርካሪ እየመታ ተራራ ላይ እንደ ዝንጀሮ እንዲመሽግ በማስገደድ በፈለገው ሰሃት፣ በተመቼው ቦታ እየደበደበ ሙትና ቁስለኛ ማድረጉን ቀጥሎበታል። እንደተለመደው ዛሬም ህዳር 22/2018 ዓ.ም የጠላት ሀይል ቲሊሊ ከተማ ዘራብሩክ ተብሎ ሚጠራው  አካባቢ  የጀግኖችን እንቅስቃሴ በመስማት ቦታ ቦታ ይዞ እየጠበቀ ባለበት ከቀኑ 10:00 ላይ የ44ኛ ክፍለ ጦር ነበልባሎች ተልበው በስተኃላው  መኻል ከተማ በመግባት መብረቃዊ ጥቃት በመፈፀም የጣለውን ጥሎ 5 ቁስለኛ አንጠልጥሎ ባገኘው መውጫ ቀዳዳ ፈርጥጦ አሲንዳቦ ካምፕ እንዲመሽግ አድርገውታል። ቁሞ መግጠም የማይችለው ወንበዴ ፣ የእናቶችን ጓዳ የሚያወድመዉ ዘራፊ፣ሴቶችን ደፋሪ ጡት ቆራጭ፣ አዛውንት ገዳይ፣ወጣት ጨፍጨረፊ ብልት ቆራጭ አረመኔ ቡድን በሰራው ልክ እየተከፈለው ቀጥሏል። #ላናሸንፍ_የጀመርነው_ትግል_የለም_ድላችን_ቅርብ_ነው💪 ©የ44ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት   ፋኖ አለበል አወቀ። #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 22/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
👍 78 63👏 7
🔥#አራት_አድማ_ብተና_ተወገዷል‼              #ቲሊሊ‼ አፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ  ክፍለ ጦር ቲሊሊ ከተማ ቦታ የያዘዉ ሆድ አደር አድማ ብተና በፊት ሲጠብቅ በጀርባው በመግባት 4ቱ በማስወገድ 5ቱ ከባድ ቁስለኛ አድርጓቸዋል። ልማደኛው 44ኛ ክፍለ ጦር በተደጋጋሚ የጠላትን አከርካሪ እየመታ ተራራ ላይ እንደ ዝንጀሮ እንዲመሽግ በማስገደድ በፈለገው ሰሃት፣ በተመቼው ቦታ እየደበደበ ሙትና ቁስለኛ ማድረጉን ቀጥሎበታል። እንደተለመደው ዛሬም ህዳር 22/2018 ዓ.ም የጠላት ሀይል ቲሊሊ ከተማ ዘራብሩክ ተብሎ ሚጠራው  አካባቢ  የጀግኖችን እንቅስቃሴ በመስማት ቦታ ቦታ ይዞ እየጠበቀ ባለበት ከቀኑ 10:00 ላይ የ44ኛ ክፍለ ጦር ነበልባሎች ተልበው በስተኃላው  መኻል ከተማ በመግባት መብረቃዊ ጥቃት በመፈፀም የጣለውን ጥሎ 5 ቁስለኛ አንጠልጥሎ ባገኘው መውጫ ቀዳዳ ፈርጥጦ አሲንዳቦ ካምፕ እንዲመሽግ አድርገውታል። ቁሞ መግጠም የማይችለው ወንበዴ ፣ የእናቶችን ጓዳ የሚያወድመዉ ዘራፊ፣ሴቶችን ደፋሪ ጡት ቆራጭ፣ አዛውንት ገዳይ፣ወጣት ጨፍጨረፊ ብልት ቆራጭ አረመኔ ቡድን በሰራው ልክ እየተከፈለው ቀጥሏል። #ላናሸንፍ_የጀመርነው_ትግል_የለም_ድላችን_ቅርብ_ነው💪 ©የ44ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት   ፋኖ አለበል አወቀ። #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 22/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
1
Photo unavailableShow in Telegram
🔥#አስደናቂዉ_ኦፕሬሽን_ቲሊሊ‼ ልማደኞቹ 44ኛ ክ/ጦር ቲሊሊ ከተማ የሰፈረዉን ሆድ አደር አድማ ብተና ጭቃ አድርገዉታል‼ በዝርዝር .....! #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 22/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
121🙏 27👍 19👏 14
Photo unavailableShow in Telegram
🔥#እየመጡ_ነው‼️ አማራነት እንደ ንስር ታድሶ ከአማራ ምድር (#ከሸዋ_ጠቅላይ_ግዛት!!) #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 22/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
👍 126 74💔 23😢 15😡 15
🔥ባለ ስናይፐሩ ከነሙሉ ትጥቁ የአማራ ፋኖን ተቀላቀለ‼️ የብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ሆኖ ሲያገለግል የነበረው አስር አለቃ ደጉ ከ48ኛ ክፍለ ጦር አንደኛ ሻለቃ የአገዛዙን ግፍና መከራ በመፀየፍ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነዉ ፅጌ ኮር ክንፍ የሆነውን ተከዜ ክፍለ ጦርን አንድ መገናኛ ሬድዮን ጨምሮ ስናይፐር ከነ መሉ ትጥቁ በመያዝ ህዳር 22/2018 ዓ.ም ተቀላቀለ። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ  ቢሆነኝ ቢያበይን መረጃውን አድርሷል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!! ©የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ      #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 22/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
91👍 29🙏 13🎉 4💔 1
Photo unavailableShow in Telegram
🔥#ሻይ_ሽጣ_ዉሃ_አፍልታ_ምትተዳደረዉ #እናት_የደም_እምባ ‼😭 አሳዛኟ በመከላከያ የተዘረፈችዋ እናት በሰከላ ወረዳ ጉንድል ከተማ‼  ሻይ ሽጣ፡ ዉሃ አፍልታ የምትተዳደረዉ እናት ከሊጥ እስከ ዱቄት፣ ከአስቤዛ እስከ ብርጭቆ  በመከላከያ ተዘርፋ የደም እምባ ታነባለች። እንዲህም ትላለች "እውነት ወታደርነት፣ ሀገር ጠባቂነት፤  የድሃ እናቶችን ደካማ በር በሰደፍ ሰርድሞ፤ ቤት ያፈራዉን አውድሞ፣ ሊጥ ደፍቶ፣ ዱቄት በትኖ፣ ብርጭቆ ከስክሶ፣ ሻይ አፍልቶ፣ ጠላ ሽጦ እንዳይተዳደር መከልከል ነዉን!? ይህ ከተማ ፋኖም ያልፍበታል መከላከያም ያልፍበታል ከዛ ዉጭ ከኛ ጋ ምን ያገናኘዋል? ለመዘረፍ ለመደብደብ ለመወደም ለመሰደድ የሚያበቃን? ደካማ እናቶችና አባቶች ተወልደዉ ባደጉበት ቀየ በደካማ አቅማቸዉ አርሰዉ ቆፍረዉ እንዳይተዳደሩ፣ ቤቱን አውድሞ፣ ሀብቱን ቀምቶ ለልመና ጎዳና እንዲወጡ ማሳደድ ነዉን!? እዉነት የሀገር መከላከያ ማለት ይሄ ነዉ? ጉልበቴ በከዳኝ፣ አቅም ባጣሁበት ፤ ኑሮ በተወደደበት ከሰል ለብሸ ያፈራሁበትን ጥሬት መዝረፍ ነዉ ወይ አላማቸው? ምናለበት ጠላቴ ያለዉን አካል ለይቶ ቢገጥም። እኛ ደካሞች ነንስ ወይ የበቀል መወጫ ምንሆነው? ጠላቴ የሚለዉ አካልስ የመሳሪያ ባሩድ ከሚደርስበት አፍንጫው ስር ተቀምጦለት አደለ ያለ ለምን ሂዶ አይገጥምም። ይሄ ነዉ ወንድነት፣ይሄ ነዉይ ጀግንነት፣ የመከላከያ መገለጫስ ይሄ ነውን? እያለች ታነባለች። እኔኮ የተከፈተ ጉሮሮየን ዘግቼ ስለማደር ምንጨነቅ እንጂ ስለ ፖለቲካ ምንፈጠፈጥ አደለሁም። በእዉነቱ እባካችሁ ቀምሸ ልሼ ማድረዉ ምተዳደረዉ ምንም የሌለኝ ድሃ ነኝና የወሰዳችሁትን እቃና ዱቄት ሰላሳ ሺ ብር የጨረስኩበትን እህል መልሱልኝ ስትል ወደ አንድ ባንዳ ሚኒሻ ደውላ ትለምናለች😭 #ይህ #ደረቅ_ሃቅ_ነው‼ትዝብቱን ለእናተ ተዉኩት......‼ #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 22/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
💔 69 61😢 13🙏 8👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
⚫️#አሳዛኝ_ዜና‼️ ዐራት ዐይና ቆሞስ አባ ይባቤ በላይ የትርጓሜ መጻሕፍት፣ የአቡሻኽር፣ የፍትሐ ነገሥት እና የቅኔ መምህር፤ በሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት የክብረ ደናግል ናዳ ቅድስት ማርያም ገዳም አበምኔት የሆኑት አራት አይናው መምህር ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። "ገዳሙን የሚመራ - በጉባኤ ቤቱ የሚያስተምር መምህር ፈልጉ" የየንታ ይባቤ የቅርብ ጊዜ መልዕክት ነበር። ምክንያቱም አገዛዙ አስሮ ከፈታቸው በኋላ እንደበፊቱ ሙሉ ጤነኛ አልነበሩም💔 ዛሬም ያ ሰው በላ አገዛዝ ኃይል ቆሞስ አባ ይባቤ በላይ ይኖሩበት ወደነበረ ቀጠና በለሊት ተጠግተው ማደራቸውን የንስር አማራ ምንጮች ገልፀዋል። በየኔታ ይባቤ በላይ እረፍተ ሥጋ የተሰማንን ኃዘን እየገለጽን ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው፣ ለገዳሙ መነኮሳትና መነኮሳይት መጽናናትን እንመኛለን።
Mostrar todo...
💔 228😢 79 59🙏 24👍 7🎉 4🏆 1
🔥ወጣቱ ሁለት የአገዛዙ ወታደሮችን አንገት አንቆ ባህር ውስጥ በመስጠም የአጥፍቶ ጠፊ እርምጃ ወሰደ‼️ ዮናስ ክንፈ ይባላል። ገና የ24 አመት ወጣት ነበር። ተወልዶ ያደገው አንጎት ወረዳ 01 ቀበሌ ውስጥ ነው። በዚህ ወረዳ ከዚህ ቀደም የወረዳው የሚኒሻ ፅህፈት ቤት ኃላፊ በፋኖ መገደሉ ይታወቃል። ከሚኒሻው ግድያ ጋር ተያይዞ ዮናስ ክንፈን የአገዛዙ ወታደሮች ከቤቱ አፍነው በመውሰድ ያሰቃዩታል። ለአንድ ወር ሲያሰቃዩት ከርመው ምንም አይነት የወንጀል ፍንጭ ሲያጡበት ከአንድ ወር እገታ በኋላ ተለቆ ወደ ትውልድ ቀየው ተመለሰ። ፀረ አማራው ኃይል፡ ዮናስን"መልክህ አላማረንም" በሚል ሰበብ እንደገና የክፋትና የስቃይ መረቡን ያጠምድበታል። ዮናስ የአረመኔዎችን እንቅስቃሴ ተመልክቶ አካባቢውን ለቆ ተሰወረ። ሌላ ቦታም የቀን ስራም ቢሆን እየሰራ ለመኖር የትውልድ ቀየውን ለቆ ተሰደደ። ዮናስ ሀገር ለቆ መሰደዱን የሰማው የብልፅግና ኃይል፡ የዮናስን አባት ከመኖሪያ ቤታቸው ሂዶ በማፈን ለእስር ይዳርጓቸዋል። ዮናስ የአባቱን በአረመኔዎች እጅ መውደቃቸውን ሲሰማ እራሱን በአባቱ የስቃይ ቦታ ላይ ለማድረግ ወስኖ ወደ አረመኔው የአገዛዙ ሰራዊት መጥቶ እጅ ሰጠ። የፋሽስቱ ዐብይ አህመድ ገዳይ ወታደሮች ዮናስን እደተራበ ጅብ እያፋሸጉ ተቀበሉት። ዮናስን ልብሱን አስወልቀው እርቃኑን አቁመው ለመስማት የሚሰቀጥጥ፡ ለማየት የሚዘገንን ግፍ ፈፀሙበት። እጆቹን የፍጥኝ ወደኋላ አመሰቃቅለው 8 ቁጥር እስር ካሰሩት በኋላ በገላው ላይ በእሳት የሚነድ ላስቲክ  አንጠባጠቡበት። በላስቲኩ የእሳት ጠብታ ተቃጥሎ ስጋው ቀልጦ አጥንቶቹ ጠቁረው እስኪታይ ድረስ እጅግ ከባድ ግፍ ፈፀሙበት። በመጨረሻም ዮናስ፡ ከዚህ ስቃይ ይገላገል ዘንድ ጨፍጫፊዎቹን "የደበቅኩት መሣሪያ አለኝ እሱን ልስጣችሁ ወደ ደበቅኩበት ቦታ ውሰዱኝ" ይላቸዋል። ደብዳቢዎቹም ለአለቃቸው ሂደው ይነግሩታል። "ጥሩ መሳሪያውን አምጡት ይሄማ ጥሩ ብር ነው። ሽጠን ወደ ኪሳችን እናደርጋለን። ከዚህ ጦርነትኮ ያለን ትርፍ ገንዘብ ነው።ሰለዚህ ከደበቀበት ቦታ ያሳያችሁና መሣሪያውን አምጡ" የሚል መልክት ሲሰጣቸው ዮናስን በላስቲክ የተቃጠለ አካላቱን ልብስ አልብሰውና ሸፍነው መሳሪያውን ከቀበረበት ቦታ እንዲወስዳቸው አደረጉት። ዮናስ አንድ ውሳኔ በልቡ ወስኗል። በጋዞ ከሚገኝ እግድ ባህር ከሚባል ቦታ ላይ እንደደረሱ መንገዳቸው በባህሩ ዳርቻ ነበር። ዮናስ፡ ከተከተሉት ሶስት የመከላከያ ሰራዊት አባላት መካከል የሁለቱን ወታደሮች አንገት አንቆ በመያዝ ወደ ጥልቁ ባህር ይዟቸው ሰጠመ። ዮናስ ገዳዮቹን ገሎ ራሱን ከስቃይ ታድጎ የፀጋ፣ የክብር፣ የጀግና ሞትን ሞተ። ሦስተኛው የመከላከያ ሰራዊት አባል፡ ዮናስ ሁለቱ ጓዶችህን ባህር ገፍትሯቸው እሱም ሲገባ አንተ ምን አየሰራህ ነበር በሚል ትጥቅ እንዲያወርድ ተደርጎ ተረሽኗል። የሁለቱ መከላከያ ሰራዊት አባላት አስከሬን እና የዮናስ ክንፍ አስከሬን ከሰጠሙበት ባህር በስምንተኛው ቀን ተንሳፎ ታየ። የአገዛዙ ወታደሮች የራሳቸውን አስከሬን ከባህሩ አውጥተው ከቀበሩ በኋላ የዮናስን አስከሬን አናስወጣም በሚል የከለከሉ ቢሆንም፡ የአከባቢው ማሕበረሰብ "ከዚህ በላይ ምን ልታደርጉት ነው?" በሚል ቁጣና እቢተኝነት የዮናስን አ*ስ*ከ*ሬን ከባህሩ አውጥተው  ተወልዶ ባደገባት መንደር የጀግና ስርዓተ ቀብር ፈፀሙለት። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ©በአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የደጋው መብረቅ ኮር ሕዝብ ግንኙነት ክፍል! #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 21/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
204💔 43👍 17🙏 17😢 11🎉 4👏 3🏆 1
Photo unavailableShow in Telegram
🔥ትግል የምትታገለው ብቻ ሳይሆን የምትጠብቀውም ነው‼️     ከሰሞኑ ሰንፈጥ ያለ የማጥራት ስራ በመጀመራችን ሀቀኛ ታጋይና ህዝቡ በደስታ እየደገፈን ነው። በአንፃሩ ወመኔዎችና ቀላዎጭ ሾተላዮች እየለየላቸው ነው።ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል በአጭር ጊዜ ታጥበን ተለቃልቀን የህዝብ ሮሮ የማይደመጥበት ሁነት እንፈጥራለን። በተጀመረው ጥልቀት ያለው ምርመራና ጠንከር ያለ ርምጃ የነጋበት ጅብ በቀኝ በግራ እየተራወጠ ቀድሞ ባዘጋጀው ጎሬ ዘሎ እየገባ ነው። ጥልቅ የማጥራት ርምጃው ተጠናክሮ ይቀጥላል።ህዝብን የሚያማርሩ የትግላችን ጥገኞች መመንጠር በመጀመራቸው በአንዳንድ አካባቢዎች አንፃራዊ አዎንታዊ ለውጦች ተስተውለዋል።      ጥልቅ እርምቱ የህዝብ ቅሬታ ከመፍታትና የውስጥ ንፅህናን ከማስጠበቅ በላይ ትግልን በመጠበቅ በኩል ሁነኛ ፋይዳ ያለው መሆኑ ታምኖበት እየተከወነ ነው።ተጠናክሮም ይቀጥላል።     ከጥገኞች ጋር የዓላማ ትስስር ያላቸው ሁሉ ሳይጠሩ አለን ብለው ሲመጡ ይስተዋላል።ይህ የተንኮል ትስስር  በጣጥሰን አሽቀንጥረን ከመጣል የሚገታን አንዳች ምድራዊ ኃይል ግን የለም።          ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!           © ዮሐንስ ንጉሱ ሙጨ #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 21/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
111👍 37💔 6😍 3🏆 2💯 1
🔥ባለሽርጡ ክፍለጦር ለተከታታይ ሁለት ቀናቶች ተጋድሎ በማድረግ ድል አስመዘገበ‼️ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ምስራቅ አማራ ኮር 1 ባለሽርጡ ክፍለ ጦር በሰሜን ወሎ ሀብሩ ወረዳ ቁጥር 8 ጠዶት በተባለው አካባቢ የመጣው የአብይ አህመድ አራዊት ሰራዊት ጋር በተደረገው ተጋድሎ አይበገሬው የባለሽረጡ ክፍለ ጦር ኮማንዶ ፋኖዎች ከህዳር 19 እስከ ህዳር 21/2018 ዓ.ም ሲቀጠቅጡት ዉለዉ አድረው ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ወደመጣበት እንዲመለስ በማድረግ ድል አስመዝግበዋል:: በመርሳ አቧሬ ገብርኤል ቤተ ክረስቲያን ከ16 በላይ አስከሬኑን በጅምላ ቀብር ሲፈፅም በመርሳ ሆስፒታል ቁጥሩ በዉል ያልታወቀ ቁስለኛ በህክምና ላይ ይገኛል:: በዚህም የመርሳ ከተማና አካባቢው ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የህክምና ቦታው በመጨናነቁ የተነሳ በመጉላላት ላይ ይገኛሉ። በዚህም የተበሳጨው የመከላከያ አዛዥ ሚሊሻዎችን እናንተ ናችሁ መረጃ ያወጣችሁብኝ በማለት ከአራት በላይ ሲረሽን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ሚኒሻ እንደታሰረ የውስጥ መረጃችን አድርሶናል። የጠላት ሰራዊት ጠዶት ሚካኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ምሽግ ምሶ ውጊያ በማካሄድ ለሃይማኖቱ ክብር እንደለለው አሳይቷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ©አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 21/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
82👍 6
🔥#የድሮን_ቅኝት_መረጃ‼️ ገደብ,መጠያ ሙሉ እናርጅ እናውጋ ቀጠናና አካባቢው የድሮን ቅኝት አለ ጥንቃቄ ይደረግ‼️ #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 21/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
👍 76 39🙏 6
🔥ተልዕኮ በመውሰድ ወደ ጠላት ቤት ተቀላቅሎ የነበረው ፋኖ ሁለቱን የብልጽግና ሚሊሻ አመራሮችን በማስወገድ ተመለሰ‼️ ፋኖ ተስፋው ይባላል። አስቀድሞ የበረኸኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃ አባል የነበረ ሲሆን ከጥቂት ወራት በፊት ተልዕኮን በመቀበል ወደ ብልጽግናው ቤት ጎራ ብሎ በመቀላቀልና በመመሳሰል አስፈላጊውን መረጃ ለወገን (ለፋኖ) ሲሰጥ ከቆየ በኋላና ሌሎችንም ተልዕኮዎች ሲፈጽም ከቆየ በኋላ በመጨረሻ አንድ የሚሊሻ ጠርናፊና አንድ ሻምበል መሪን ካስወገደ በኋላ ግዳጁን በመወጣት ወደ 14ኛ ክፍለ ጦር በረኸኛው ጅበላ ሙተራ ሻለቃ ተቀላቅላል። በተያያዘ ዜና ወርቁ አወቀ የተባለው የመከላከያ ተብየ አባል ከ32ኛ ክፍለ ጦር ወደ በረኸኛው ቀስተ ደመና ሻለቃ ከነ ሙሉ ትጥቁ ተቀላቅሏል። ህዳር 21/2018 ዓ.ም ድል ለአማራ ፋኖ! ©ፋኖ ዘመን ባሳዝነው የ14ኛ ክፍለ ጦር ሕዝብ ግንኙነት #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 21/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
111👍 15🙏 13😢 2
Photo unavailableShow in Telegram
🔥''#ምነው_መጣን_ብለው_ቀሩሳ❓' ያልከው ሰውዬ - እስኪመጡልህ ድረስ ተከታዮቹን ጥያቄዎች እየመለስክ ጠብቃቸው‼️ ✅ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ መሀል ሀገር ላይ ያውም 2 አመት ባልሞላ ጊዜ ራሱን አደራጅቶ ፣ አሰልጥኖና አስታጥቆ እንደአማፂ ቡድን ሳይሆን እንደመንግስት ግዙፍ የሆነ ሰራዊት የገነባ ከፋኖ ውጪ አንድ የትጥቅ ትግል ድርጅት ልትነግረኝ ትችላለህን? ✅ ባለፉት 50 አመታት ውስጥ እንኳ ከተነሱ የትጥቅ ትግል ድርጅቶች ውስጥ ኦነግ 40 አመት ኤርትራ ጫካ ለጫካ ሲሄድ ከኢትዮጵያ አንድ ወረዳ ተቆጣጥሮ ለወራት እንኳ የቆየበትን ዘመን ትነግረኛለህን? ✅ ግንቦት -7 ወይም አዴኃን አለያም ሌላ ድርጅቶች ተጨፍልቀው የፋኖን አንድ ክፍለ ጦር እንኳ ይሞሉ ይሆንን ? በአመታት የኤርትራ ቆይታቸው ማይካድራን ተሻግረው የመጡበትን ጊዜስ ልታስታውሰኝ ትችላለህን? ✅ ከዋና ከተማ ከ20-30 ኪ.ሜ ርቀት ተጠግቶ መዋጋት አይደለም ይቅርና የአንድ ቀበሌ ጎጥ ተቆጣጥሮ የምታስታውሰው ታጣቂ ሀይል ታስታውሳለህን ? ✅ አይደለም ለ3 አመታት ያለእረፍት መደበኛና የሽምቅ ውጊያ እያደረገ አቅሙንም በየእለቱ እያጎለበተ የተጓዘ ቀርቶ ለ3 ሰአት ከኢህአዴግ አገዛዝ ጋር ሲዋጋ የምታስታውሰው ኃይልስ ይኖር ይሆንን ? ✅ ህወሓትስ ከአመታት የትግል ሂደት በኃላ እግሩን ከትግራይ ክልል ያወጣው ኢህዴንና ኦህዴድ የሚባሉ ጫማዎችን ሰርቶ አይደለምን? እነዚህን መረማመጃ ጫማዎቹን ተጠቅሞ ወደ  መሀል ሀገር እስከሚገባ 17 አመታት አልፈጀበትምን ? #ፋኖን የምንተቸው ትግሉ ፋታ የማይሰጥ፣ አይን የማያስከድን፣ በይደር የማይተው 'የህልውና ትግል' በመሆኑ ''ተቋም'' ሆኖ ፣ ከአውደ ውጊያ ይልቅ ስትራቴጂካዊ ድልን የሚቀዳጅበትን ትልቅ አቅም እንዲፈጥር ከመሻት እንጂ በአጭር ጊዜ የተጓዘው ርቀት ''ተአምር'' የሚባል መሆኑ ከማንም የተሰወረ ሆኖ አይደለም! እናማ '' #መጣን_ብለው_ቀሩ'' እያልክ ሙድ ለመያዝ ከመሞከርህ በፊት እጣገብህና መሀል ሀገር ያለ ሀይል መሆኑን ልታስታውስ ግድ ይልሀል። ከኤርትራ ተነስተው አይደለምና የሚመጡት! በነገራችን ላይ ሁሉንም ነገር ትተነው 👉 For any unti-government rebel group 'existence' by itself a victory. ለአገዛዙ ደግሞ የታጣቂ ቡድኖች መኖራቸው ብቻ ከሽንፈት ይቆጠራል! '' 10 ኃላቀር መሳሪያ የታጠቁ ጃውሳዎችን በ10 ቀን ቀበቶ እናስፈለን'' ተብሎ የተጀመረውን ጦርነት ዛሬ 3ተኛ አመቱ ላይ በተቃራኒው ሀይል በኩል የፈጠረውን ግዙፍ አቅምና ንቅናቄ መገንዘብ ካልቻልክ እውነትም ስቡ ደፍኖሀል ማለት ነው! የአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ሂደቱ ላይ ምንም አይነት ችግር ቢኖርበትም እንኳ ፣ የተነሳበት ሀቀኛና የማይታበል ኮዝ ወደፊት እንጂ ወደኃላ የሚመልሰው አይሆንም!           ✍ዘሪሁን ገሰሰ #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 20/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
211👍 60🫡 12🎉 7🏆 3
02:49
Video unavailableShow in Telegram
🔥እሸት ክፍለ ጦር ለወራት ያሰለጠናቸዉን የፋኖ ሰራዊቶች በዛሬዉ ዕለት በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ‼️ አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒልክ ዕዝ ላስታ አሳመነዉ ኮር እሸት ክፍለ ጦር ለተከታታይ ወራት ያሰለጠናቸዉን ፋኖወች በዛሬዉ ዕለት ማለትም ህዳር 20/2018 ዓ.ም አስመርቋል። ተመራቂ ፋኖወችም ለወራቶች በአካል ብቃት፣ በተኩስ ፣ በሰልፍ እና ወታደራዊ ሳይንሱ የሚጠይቀውን እውቀት እና ጥበብ ቀስመዉ ተመርቀዋል። በዚህ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይም የነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ አዛዥ ሻለቃ ደምሌ ጣፋጭ (ጥንቅሹ) ጨምሮ የላስታ አሳመነዉ ኮር ከፍተኛ አመራሮች እና የእሸት ክፍለ ጦር አመራሮች ተገኝተዉ መልዕክት አስተላልፈዋል። ተመራቂዎቹ የፋኖ አባላቶችም እኛ  የህልውና ትግሉን በድል ለማጠናቀቅ ብቻ ሳይሆን ስለ ነገይቱ ኢትዮጵያ አስበን ጭምር ነዉ የሰለጠነዉ ብለዋል። ሰልጣኞቹ አክለዉም እኛ ሰልጥነን ለዚች እለት ስንበቃ እኔ ጎጃም፣ እኔ ጎንደሬ፣ እኔ ሸዋዬ፣ እኔ ወሎዬ እንድንል ሳይሆን አንድ ሁኑ የሚለውን የጄኔራል አሳመነው ፅጌ የኑዛዜ ቃል አክብረን  በአማራነታችን ፀንተን እንቆማለን ሲሉ ተናግረዋል። በመጨረሻም ተመራቂዎቹ የተሰጣቸዉን አደራ በአግባቡ እንደሚወጡ ቃለ መሃላ በመፈፀም ቃል ገብተዋል። አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒልክ ዕዝ ላስታ አሳመነዉ ኮር ሚዲያ እና ኮሚኒኬሽን ክፍል ኃላፊ ጋዜጠኛ  ፋኖ ደረበ መኮንን! "ሰልጥነን እንዋጋለን እየተዋጋን እንሰለጥናለን!" መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን! ©የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ሚኒልክ ዕዝ #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 20/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
22.02 MB
97👍 30👏 6🎉 6
45👍 10👏 4
🔥አማራ ጠሉ የአብይ አህመድ ወንበር ጠባቂ ኃይል ለልማት በወጣ ሕዝብ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አደረሰ‼️ ራሱን ጥምር ጦር ብሎ የሚጠራው የአማራ ጠሉ አብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ ኃይል በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ በመንገድ ጠረጋ ልማት በተሰማራ ሕዝብ ላይ ድንገተኛ ተኩስ በመክፈት መካናይዝድና የቡድን መሳሪያ በመጠቀም በስድስት ሰዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል:: በዚህም ፋሽስቱ የአብይ አህመድ አገዛዝ ሕዝብ ጠል ፣ ልማት ጠል ፣ ማንነት ጠልና ፍፁም ሰብዓዊነትም የሌለው መሆኑን በይፋ አረጋግጧል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ሕልውናችን በተባበሩ ክንዳችን ©የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል #ዐንድ_አማራ‼️ #ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️ #ምረር_አማራ💪 #ድል_ለአማራ_ፋኖ💪 #ድል_ለአማራ_ህዝብ💪 20/ዐ3/2018 ዓ.ም @NISIREamhra
Mostrar todo...
70😢 14💔 12👍 10
🔥#የአራቱ_ማህበራት_መግለጫ‼️ 1. የሰሜን አሜሪካ ካሪቢያን እና ላቲን አሜሪካ የሰንበት ት/ቤቶች ኅብረት፣ 2. ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል፣ 3. የማኅበረ በዓለ ወልድ በሰሜን አሜሪካ 4. ዋልድባን እንታደግ ሰሜን አሜሪካ
Mostrar todo...
80👍 3😍 3