ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)
Open in Telegram
በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
Show more2025 year in numbers

50 485
Subscribers
-624 hours
+27 days
+10030 days
Posts Archive
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ፡፡ አሜን፡፡ ✞✞✞
=>+"+ እንኩዋን ለታላቁ "ጻድቅና ገዳማዊ አባ በኪሞስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"+
+*" ታላቁ አባ በኪሞስ "*+
=>በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ "ታላቁ : ዓቢይ : (THE GREAT)" የሚል ስም የሚሰጣቸው አባቶች የተለዩ ናቸው:: አንድም እጅግ ብዙ ትሩፋቶችን የሠሩ ናቸው:: በሌላ በኩል ደግሞ በተመሳሳይ ስም ከሚጠሩ ሌሎች ቅዱሳን እንለይበታለን::
+ገዳማዊ ሕይወት ጥንቱ ብሉይ ኪዳን ነው:: በቀዳሚነትም በደብር ቅዱስ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ ደቂቀ ሴት እንደ ጀመሩት ይታመናል:: ሕይወቱ በጐላ: በተረዳ መንገድ የታየው ግን በታላቁ ጻድቅ ሄኖክ: ከዚያም በቅዱሱ ካህን መልከ ጼዴቅ አማካኝነት ነው::
+ቀጥሎም እነ ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ : እነ ኤልሳዕ ደቀ መዝሙሩ ኑረውበታል:: በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ሙሉ ሕይወቱን በገዳም (በበርሃ) ያሳለፈው መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቅድሚያውን ይይዛል::
+ለስም አጠራሩ ስግደት ይሁንና መድኃኒታችን ክርስቶስ በገዳመ ቆረንቶስ ለ40 ቀናት በትሕርምት ኑሮ ገዳማዊ ሕይወትን ቀድሷል:: አስተምሯል:: በዘመነ ስብከቱም ያድርባት የነበረችው የደብረ ዘይቷ በዓቱ (ኤሌዎን ዋሻ) በራሷ ለዚህ ሕይወት ትልቅ ማሳያ ናት::
+ከጌታ ዕርገት በሁዋላም ክርስቲያኖቹ የዓለም ሁካታ ሲሰለቻቸው: አንድም በንጹሕና በተሸከፈ ልቡና ለፈጣሪያቸው መገዛትን ሲሹ ከከተማ ወጣ እያሉ ይኖሩ እንደ ነበር የታሪክ መዛግብት ያሳያሉ:: አኗኗራቸውም በቡድንም: በነጠላም ሊሆን ይችላል::
+ዋናው ነገር ግን በጾምና በጸሎት መትጋታቸው ነው:: ይሕም ሲያያዝ እስከ 3ኛው መቶ ክ/ዘመን ደረሰ:: በዚህ ዘመን ግን አባ ዻውሊ የሚባል አንድ ንጹሕ ክርስቲያን ይሕንን ሕይወት ወደ ሌላ ደረጃ ከፍ አደረገው:: ለ80 (90) ዓመታት ሰው ሳያይ ተጋድሎ "የባሕታውያን አባት" ተባለ:: ደንብ ያለው ተባሕትዎም ጀመረ::
+ይህ ከሆነ ከ20 ዓመታት በሁዋላ ደግሞ አባ እንጦንስ የሚባሉ ደግ ክርስቲያን ይህንን ገዳማዊ ሕይወት በሌላ መንገድ አጣፈጡት:: በቅዱስ ሚካኤል አመንኩዋሽነት ገዳማዊ ሕይወት በምንኩስና ተቃኘ:: ስለዚህም አባ እንጦንስ "የመነኮሳት አባት" ተባሉ::
+እርሳቸውም ሕይወቱን ለማስፋፋት ከተለያዩ አሕጉር ደቀ መዛሙርትን እየተቀበሉ አመንኩሰዋል:: ቅዱሳን የአባ እንጦንስ ልጆችም ወደየ ሃገራቸው ተመልሰው: ሕይወቱን በተግባር አሳይተው ገዳማዊነትን አስፋፍተዋል::
=>አባ በኪሞስ ስም አጠራሩ እጅግ የከበረ: ሽምግልናው ያማረ ባሕታዊ: መነኮስና ሐዋርያዊ አባት ነው:: የነበረው በዘመነ ጻድቃን (በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን) ሲሆን ትውልዱ እንደ ብዙዎቹ የወቅቱ ቅዱሳን በላይኛው (በደቡብ) ግብጽ ነው::
+አባ በኪሞስ ከክርስቲያን ወላጆቹ ተወልዶ: በልጅነቱ ክርስትናን አጥንቶ በእረኝነት ተሰማራ:: በጐቹን ሲጠብቅም የእግዚአብሔር ጥሪ ወደ እርሱ መጣ:: ያኔም እድሜው ገና 12 ዓመት ነበር::
+አጠራሩም እንዲህ ነው:: በእረኝነት ሳለ መልአከ እግዚአብሔር ሰው መስሎ መጥቶ ተገናኘው:: ቁጭ ብሎም ስለ መናንያን ክብር ሲያጫውተው ከዋለ በሁዋላ "ለምን እኔና አንተ ለዚህ ክብር እንድንበቃ አንመንንም?" ሲል ጠየቀው::
+ሕጻኑ በኪሞስም ደስ ብሎት "እሺ!" አለው:: ወዲያውም መንጋውን ለወላጆቹ መልሶ ከመልአኩ ጋር ወደ ገዳም ሔዱ:: ቅዱሱ መልአክም በመንገድ ሳሉ ብዙ ምሥጢራትን ነገረው:: አጸናው:: ረድኤተ እግዚአብሔርንም አሳደረበት::
+ልክ ወደ አንድ ገዳም ሲደርሱ ግን ተሰወረበት:: ቅዱስ በኪሞስም ወደ ገዳሙ ገብቶ ይምናኔ ሕይወትን ጀመረ:: በዚያም እንደ ልጅነቱ አበውን እያገለገለ: ሥርዓተ ገዳምን: ትሕርምትን: አርምሞንና ተጋድሎን በደንብ አጠና::
+በዚያው ገዳም ሳለም ምንኩስናን ተቀበለ:: ለ24 ዓመታት አገልግሎ 36 ዓመት በሞላው ጊዜም ተባሕትዎን ተመኘ:: ከአባቶች ዘንድ ተባርኮም ጭው ወዳለው በርሐ እየዘመረ ተጉዋዘ::
+አንዲት ቦታ ላይም የቀኑን ሐሩር: የሌሊቱን ቁር ሳይሰቀቅ ለ3 ዓመታት ጸለየ:: እድሜው 39 ዓመት ሲሆን እንደ ገና ጭራሽ ፍጥረት ወደ ማይደርስበት በርሃ ተጉዞ ደረሰ::
+የደረሰበት አካባቢ ፀሐይ እንደ እሳት የምታቃጥልበት: ምድር እንደ ብረት ምጣድ የጋለችበት ነው:: ቸር እግዚአብሔር ግን ለዚህ ታላቅ ሰው አንዲት የተምር ዛፍ አበቀለለት:: ትንሽ ምንጭንም አፈለቀለት::
+አባ በኪሞስም ዋናውን ተጋድሎ በዚህ ሥፍራ ጀመረ:: ጾምን : ጸሎትን : ስግደትን ያዘወትር ነበር:: ጾሙ በመጀመሪያ 3 ቀን: ቀጥሎ 7 ቀን: በመጨረሻ ግን በ40 ቀን አንዴ ብቻ ማዕድ የሚቀምስ ሆነ::
+ለዛውም ምግቡ አንዲት እፍኝ ይቆረጥማል:: አንዲት ጉንጭ ውሃን ይጐነጫል:: ከዚህ በላይ ለሥጋው ምክንያትና ምቾትን ሊሰጣት አልፈለገም:: በዚህም ምክንያት አካሉ ደርቆ ከሰውነት ተራ ወጣ:: ግን ብርቱና ደስተኛ: የማይደክምም ተዋጊ ነበር::
+የሚገርመው ደግሞ ጸሎቱ ነው:: ሌሎች ጸሎቶቹ ሳይቆጠሩ በመዓልት (በቀን) 2,400 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን በልዩ ተመስጦ ያደርሰው ነበር:: በሌሊትም በተመሳሳይ ቁጥር ይደግመዋል:: በድምሩ በየዕለቱ 4,800 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት ይል ነበር::
+ስግደቱንማ ማን ቆጥሮት! ታላቁ አባ በኪሞስ እንዲህ ባለ ገድል ለ24 ዓመታት ቆየ:: እድሜውም 63 ደረሰ:: አንድ ጊዜ ግን ሕማማተ ክርስቶስን እያሰበ ያለ ምግብ ለ80 ቀናት ቆየ:: ፈጽሞ በተራበ ጊዜም ቅዱስ መልአክ ከሰማይ ሕብስተ በረከቱን: ጽዋዐ አኮቴቱን ይዞለት ወረደ::
+ከሕብስቱ መግቦት: ከጽዋው አጠጥቶት ወደ ሰማይ ዐረገ:: ሲያርግ ግን ሕብስቱን ትቶለት ነበር:: "ዘወትርም ከዚህ ተመገብ" ብሎታል:: አባ በኪሞስም ከዚያች ቀን ጀምሮ እስከ ዕረፍቱ ድረስ የተመገበው ከዚያ ሕብስት ነው:: ግን አላለቀም ነበር::
+በታላቁ አባ በኪሞስ ዘመን እነ አቡነ ኪሮስና ታላቁ ሲኖዳን የመሰሉ አበው ነበሩ:: በተለይ የባሕታውያን ሁሉ አለቃ አባ ሲኖዳና አባ በኪሞስን መንፈስ ቅዱስ እንዲህ አስተዋውቁዋቸዋል::
+አንድ ቀን አባ ሲኖዳ የእንቁ ምሰሶ ከምድር እስከ ሰማይ ተዘርግቶ ያይና "ጌታየ! ምሥጢሩ ምንድን ነው?" ቢል "ይህ ምሰሶ አባ በኪሞስ ነውና ሒድ ተገናኘው" የሚል ቃልን ሰማ:: አባ ሲኖዳም በእግሩ ተጉዞ አባ በኪሞስን አገኘው::
+ሰላምታን ከተለዋወጡ በሁዋላ አባ በኪሞስ ታላቁ ሲኖዳን "እኔ ወጥ ልሥራ: አንተ ውሃ ቅዳ" አለው:: ቅዱስ ሲኖዳ ከበር ብቅ ብሎ ማሰሮውን በተአምራት ውሃ ሞልቶት ሲመለስ አባ በኪሞስ ደግሞ ያለ እሳት ወጡን አብስሎት ቆየው::
+2ቱም ተገርመው ፈገግታን ተለዋወጡ:: ማንነታቸውንም ተዋወቁ:: ለመናፈስ ወደ በርሃ ወጥተው ሳለም ደክሟቸው ቁጭ አሉ:: ከፊታቸው አንድ የሰው ራስ ቅል ነበርና በበትራቸው መታ : መታ አድርገው "አንተ! ተነስ አጫውተን" አሉት::
+ያ አጽምም ሥጋ ነስቶ: ተነስቶ ሰገደላቸው:: "ከወዴት መጣህ?" ቢሉት "ከሲዖል" አላቸው:: አረማዊ እንደ ነበርና የሲዖልን የመከራ ብዛት ነገራቸው:: አክሎም "ክርስቲያን ነን እያሉ በክርስትናቸው የሚቀልዱ ከእኛ በታች በብዛት አሉ:: መከራቸው ተነግሮ አያልቅም" አላቸው::+ድጋሚ በበትራቸው ነክተው ወደ ነበረበት መለሱ:: ከዚያም ቅዱሳኑ ወደየ በዓታቸው ተሰነባበቱ:: ታላቁ አባ በኪሞስ ከዚህ በሁዋላ ለ7 ዓመታት ያህል መልአክ በክንፉ እየወሰደው ወንጌልን ሰብኩዋል:: ብዙዎችንም ወደ ሃይማኖትና ንስሃ
1:01:01
Video unavailableShow in Telegram
✞አባ ገብረ ክርስቶስ (ኢትዮጵያዊው ቅዱስ)
✞አባ ዮስጦስ (ዝምተኛው ቅዱስ)
✞ቅዱሳን፦ #ኒቆላዎስ #ሳዊሮስ #ጥዋሽ #ሱርስት #ተላስስ #ታውፋኔዎስ . . .
✞ቸር በዓል !
https://t.me/zikirekdusn
🔴ታኅሣሥ10
84.32 MB
✝እንኳን አደረሰነ!
✞በዓለ ቅዱሳን፦
✿ኒቆላዎስ ዘሜራ
✿ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
✿ታውፋኔዎስ ዘእስክንድርያ
✿ሱርስት ዘቁስጥንጥንያ
✿ገብረ ክርስቶስ ዘኢትዮጵያ
✿ዮስጦስ ዘደብረ እንጦኒ
✿ሜልዮስ ወታውፍያ
✿ጥዋሽ ሕጽው
✿ተላስስ ወአልዓዛር (ዘባቢሎን)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡
https://t.me/zikirekdusn
✞እንኳን አደረሳችሁ!
❖እስከነ አባ ዮስጦስ (ዝምተኛው ቅዱስ) ድረስ፤ ለቅዱሳን ሥጋና ታሪክ የተሠራውን ሳስብ በግብጻውያን ክርስቲያኖች እቀናለሁ!
❖የኢትዮጵያዊን ቅዱስ መናኝ አባ ገብረ ክርስቶስ (በኛ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ይባላሉ)፥ መጨረሻቸው አለመታወቁን ሳስብ ደግሞ ፍጹም ሐዘን ይሰማኛል!
(በ1966 ዓ/ም ኢየሩሳሌም ተቀብረዋል ፤
ወይስ ብዙዎቹ እንደሚሉት ከነሥጋቸው ወደ ብሔረ ሕያዋን ተነጥቀዋል?)
❖ለኔ ሁለተኛው ይመስለኛል! (ምክንያቱም በኢየሩሳሌም ካሉ ኢትያጵያውያን መቅበር አይደለም ፥ በአካል አየኋቸው የሚል ሰው አልተገኘምና)
✞ቸሩ መድኃኔዓለም የቅዱሳን ገብረ ክርስቶስ፥ ዮስጦስ፥ ኒቆላዎስ፥ ሳዊሮስ፥ ጥዋሽ፥ ሱርስት፥ ተላስስ፥ አልዓዛር፥ ታውፋኔዎስን በረከት ያሳድርብን!
ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)
" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር
🔗https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
Photo unavailableShow in Telegram
✝✞✝ አባ ዮስጦስ ✝✞✝ (ዝምተኛው መነኩሴ)
~እኒህ ደግ ግብጻዊ አባት ካረፉ እነሆ ዛሬ (ታኅሣሥ 10) 46ዓመት ሞላቸው::
~ጻድቁ ከተደነቀ ዝምታቸው ባሻገር "አሁን ሰዓቱ ስንት ነው?" በሚል ድንገተኛ ጥያቄአቸው ይታወቁ ነበር::
~ለቀዳሚው ሊቀ ዻዻሳት አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊም ቅርብ ወዳጅ ነበሩ ይባላል::
~አባ ሺኖዳም "እግዚአብሔር አባ ዮስጦስን በ20ኛው ክ/ዘ ያመጣቸው በ4ኛው መቶ ክ/ዘ የነበሩ ቅዱሳንን ሕይወት በገሃድ ለማሳየት ነው" ማለታቸውም ይነገራል::
~ግብጻውያን ብርቱዎች ናቸውና የአባ ዮስጦስን ታሪክ ጠርዘው : አደራጅተው : ለፊልም ሁሉ አብቅተውታል::
~እኛ ደግሞ ቅዱሳን አባቶቻችንን ለመዘከር ገና ከእንቅልፋችን አልነቃንም::
~በጸሎታቸው ሃገርን የጠበቁ ታላላቅ አባቶችን በዘመናችን ብናይም "ታሪካቸውን ማን ይጻፈው? ማንስ ያጽድቀው? ወደ ሕዝብስ እንዴት ይድረሱ?" የሚሉትን ጥያቄዎች የሚመልስ መሪና ትውልድን ይፈልጋል::
" አምላከ ቅዱሳን ከንዋመ ሐኬት (ከስንፍና እንቅልፍ) ያንቃን:: "
"" የአባ ዮስጦስ በረከትም በእኛ ላይ ይደርብን:: አሜን:: "
ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)
" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር
🔗https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
And since he was contra to the heretics, he wrote many works. And because he rebuked even Emperor Justin in public, the Emperor [and later his successor Emperor Justinian as well] decided to kill him.
✞Nevertheless, when Empress Theodora (the wife of Justinian), whose faith was upright, heard this plot, she went to the scholar in the night and told the father, “Please flee.” However, the Saint responded with, “Death is an honor to me thus I will not take to flight.” Hence, she gathered the fathers and they pleaded him, “Please for the Church” and sent him to Egypt.
✞While he was on the move, his killers went after him. And when they closed in on him on the road, he disappeared from them [as he was concealed by God]. He then went with them [hidden] for several days. And when they gave up and returned, he reached the land of Egypt.
✞And in the land of Egypt, he put away his bishopric attire and wore an old cloth of a monk and taught the people as well as the monks and consoled them. And he performed miracles in many places.
✞And when the elder monks knew who he was, they bowed down before him. And in the house of a kind person named Dorotheus, he passed away around the middle of the 6th century on Yekatit 14 (February 21). Today is the day on which the scholar’s relics were translocated.
✞✞✞Abba Yustos El Anthony – The Silent Monk✞✞✞
=>It has been 45 years since this righteous Egyptian father departed. (1910-1976 A.D)
✞The Righteous Father, beyond his admired silence, was known for his sudden question, “What time is it now?”
✞It is said that he was a close friend to the late Patriarch Abune Shenouda lll.
✞And it is told that Pope Shenouda had said about the Saint, “God rose Abba Yostos in the 20th century to show the lives of the 4th century saints vividly.”
✞As Egyptian’s are strong [in relation to the Saints]; they have compiled and organized the biography of Abba Yostos and even made it into a movie.
✞And we, on the other hand, have not woken up from our slumber to commemorate our holy fathers.
✞Though we have seen great fathers in our time that have kept the country with their prayers, a leadership and a generation is needed that will answer the questions, “Who shall write their biographies? Who shall sanction their stories? Who shall make their stories available for the people?”
✞✞✞May the God of the Saints awaken us from the sleep of idleness. And may the blessing of Abba Yostos indwell in us. Amen.
✞✞✞May the God of the Saints aid and forgive us. And may He let us partake from their blessings.
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 10th of Tahisas
1. St. Nicholas of Myra (Scholar)
2. St. Severus of Antioch
3. St. Surest the Ascetic
4. St. Tewash the Eunuch
5. Sts. Talases and Lazarus
✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Nathanael the Apostle
2. Abune Melka Kiristos
3. St. James the Apostle (Son of Alphaeus)
4. St. Helena (Helen), Empress
5. The Holy Cross
6. St. Constantine the Great
✞✞✞ “. . . it was needful for me to write unto you, and exhort you that ye should earnestly contend for the faith which was once delivered unto the saints.”✞✞✞
Jude 1:3
✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞
(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
And the matter repeated itself 3 and 4 times.And on the 4th stage, the man gained his senses and hid himself and saw the person who was doing all this compassion for him.
✞He then run and fell down before the feet of St. Nicholas. Thereafter, he said,” My father! You took my soul out of the inferno”. The Saint then counseled the man, told him his secret and returned after instructing him not to speak to anyone about what had taken place. That man, after that day, became a kind Christian.
✞And on another day, our Lord, our Lady and a holy angel descended and gave St. Nicholas presents. The angel gave him a throne, the Mother of Light gave him a clothing of light and the Lord granted him His Gospel.
✞Immediately after that, the fathers came to the desert where he dwelt and ordained him to become the Bishop of Myra. And because the era was the Era of Persecution, he strengthened the people of Myra for martyrdom and accomplished his responsibility.
✞However, when the accounts of his life reached the Emperors, they brought him for judgement. And for the sake of Christ, he was accused of preaching about Christ, was sentenced to torture and death. Thus, they took him to the arena of testimonies and lashed him in public, burned him and shed his blood.
✞Nonetheless, because God wanted him for a different vocation, he did not die. However, they tortured him in cruelty for years. And finally, they threw him into prison. And while he was in prison, the Era of Persecution came to a close and Constantine became Emperor.
✞And at that time, the faithful had their father released and placed him on his throne. And after leading the people for 13 years, when Arius renounced, he went to Nicaea. There, he was counted as one of the 318, and before the council, he revealed a miracle.
✞In Nicaea, with his companions, he denounced Arius, made rites, wrote books and returned to his country. And after spending 40 years on his see, he passed away and was buried on this day.
✞Nicholas means “one who wins over the people.”
✞✞✞Saint Surest✞✞✞
=>This holy mother was one of the renowned mothers that rose during the Era of the Righteous. Though she was raised in a palace, she inherited from her virtuous mother goodness. And while she was in a luxurious life, she did not forget Christ - her life.
✞Because her father was loved, she was betrothed to be a wife to the sons of the Emperors at the age of 12 years. It is true that shunning riches and honor is difficult for a person of advanced age, let alone for a person of a youthful age.
✞However, St. Surest thought of an idea. And she went to her father and said, “Allow me to make a pilgrimage to salute different parishes before I am wed.” And when he responded with, “After your wedding” she replied, “I have made a vow to my Creator to salute His tomb while a virgin.”
✞Hence, her father sent her on her way with 300 dinars of gold to Jerusalem accompanied by many soldiers. There, that holy child after saluting/kissing the tomb of the Lord, escaped from the soldiers. Then, after that, no one knew where she was. However, Surest went from Jerusalem to Egypt and had a monastery built with the gold.
✞But she became a nun and entered the desert. There, she fought for 27 years without seeing anyone, in austerity, suffering and silence.
✞However, one day, a priest named Silas, who brought food for the hermits, found her and she told him her accounts and she departed after prostrating. He then buried her on this day at the age of 39 years.
✞✞✞ St. Severus the Great✞✞✞
=>St. Severus was a father that rose in the 6th century around Antioch in Syria. The period was when the Melkites/Melchites (Duophysites) had the upper hand [in rule] and the flight of Orthodox Miaphysites took place and [it was also an era when] their numbers were diminished. It was at this juncture that the great scholar St. Severus came forth by the will of God. The scholars [of the Church] call him a “lion”.✞The Saint had endured much for the Tewahedo (Miaphysite) Faith.
Memhir Esuendale:
#Feasts of #Tahisas_10
✞✞✞On this day we commemorate Abba Nicholas, Abba Severus and Saint Surest✞✞✞
✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞
✞✞✞Saint Nicholas the Scholar✞✞✞
=>Saint Nicholas
* was zealous to his faith,
* was a scholar, who had an upright conduct,
* was a martyr that received much tribulation,
* was an apostle that converted many,
* was a righteous that fought in the desert for years,
* was a shepherd that served as a bishop,
*and was one of the 318 Fathers.
✞He was born in the 3rd century and his place of origin was called Myra (Mora). Though we do not know where this place is exactly located (according to tradition), history tells us that it was part of the Roman Empire (now Demre, Turkey). The parents of St. Nicholas were good Christians of the time.
✞Though they lived following the laws and rites, partaking from the Holy Eucharist and by giving alms, they did not have a child. While they beseeched God, their youthful years passed and they became advanced in age. And they stopped asking for a child. And when they stopped pleading, God created this holy fruit in the womb of Yona (Tona).
✞And the Saint was born to the astonishment of his parents as they praised God. When he was born, their eyes witnessed a wonderful thing. When they cut the umbilical cord and bent to raise him, the Saint rose by himself and they heard him praise his Creator.
✞And for 2 hours they heard him praying a prayer, which they knew not of. It is obvious that a days old child doing such a thing is very astounding. Afterwards, the amazing things of the child, St. Nicholas, continued.
✞For example: If it was not 3 PM, on Wednesdays and Fridays, he did not suckle from his mother’s bosoms. And he always did not suckle from his mother’s left breast. And he at all times suckled only from her right breast.
✞And in such manner, St. Nicholas grew. And when he was youthful, his elderly parents left him much riches, 400 gold dinars and the like, and they passed away. Nevertheless, he left everything and entered into the desert at the age of 16 years.
✞And there, the fathers that saw him fast, pray and prostrate, used to be amazed. That was because he was fast like a wheel when he worked, followed orders or prostrated. It is truly unbelievable that he did this in his child’s physique. And because he completed the upright teachings of the faith speedily, he was ordained a priest just at 19 years.
✞After he was ordained a priest, he expanded his strife and service. And making the monastery his starting place, he used to cover many areas by preaching. And in his evangelic mission, he used to perform many miracles. Particularly on one day, he has fed the people of an area miraculously as his Creator by blessing a small portion of bread that they had.
✞And a great amount of the leftover was removed in baskets. (John 6:5) As our Lord had said, “He that believeth on me, the works that I do shall he do also” (John 14:12). The Saint healed the sick and raised the dead for years as well.
✞One day, while he was in his cell, he knew that one previously affluent man and 4 of his daughters were to lose their lives. And the reason was because Satan had whispered to this rich man who had lost his wealth and had become a destitute to do wicked deeds, who lived in the city around the Saint. The man prepared 4 houses for his 4 daughters and readied to sell them for prostitution.
✞And St. Nicholas that knew this by grace, thought “Aid is comes prior to reproving” and without being seen in the night, took 100 dinars of the 400 that his parents left him and dropped it at the door of the man and hid. And the man amazed, stopped his sinful thought.
✞Again the Saint knew that the idle man after completing the money was about to do the same thing yet again. For a second time, hiding himself, he dropped for him a 100 more dinars.
+*" ✝ታላቁ ቅዱስ ሳዊሮስ "*+✝
=>ቅዱስ ሳዊሮስ በ6ኛው መቶ ክ/ዘመን መጀመሪያ አካባቢ በሶርያ አንጾኪያ የተነሳ አባት ነው:: ወቅቱ መለካውያን (2 ባሕርይ ባዮች) የሰለጠኑበት እንደ መሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናን ያነሱበትና የሚሰደዱበት ጊዜ ነበር:: በዚህ ጊዜ ነበር ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ሳዊሮስ በሥላሴ ፈቃድ ለቤተ ክርስቲያን የተነሳው:: ሊቃውንት አንበሳ ሲሉ ይጠሩታል::
+ቅዱሱ ለተዋሕዶ ብዙ ሆኖላታል:: የመናፍቃን ጸር በመሆኑ ብዙ ድርሰቶችን ደርሷል:: ንጉሡን ዮስጢያኖስን (Justinian) ሳይቀር በይፋ ይገስጸው ነበርና ንጉሡ ሊገድለው ቆረጠ::
+ሃይማኖቷ የቀና ንግሥቲቱ ታኦድራ ግን ይህንን ስትሰማ በሌሊት ወደ ሊቁ ሒዳ "እባክህን ሽሽ" አለችው:: እርሱ ግን "ሞት ለእኔ ክብር ነውና አልሔድም" ሲል መለሰላት:: አባቶችን ሰብስባ "ስለ ቤተ ክርስቲያን ስትል" ብለው ለምነው ወደ ግብጽ ሸኙት::
+እርሱ እየሔደ ገዳዮቹ ያሳድዱት ገቡ:: መንገድ ላይ ቢደርሱበትም ተሰወረባቸው:: ለብዙ ቀናትም አብሯቸው ተጉዋዘ:: እነርሱ ተስፋ ቆርጠው ሲመለሱ እርሱ ግን ምድረ ግብጽ ደረሰ::
+በምድረ ግብጽም የዽዽስና ልብሱን ትቶ የመነኮሳትን አሮጌ ልብስ ለብሶ ሕዝቡንና መነኮሳቱን አስተማረ: አጸና:: በየቦታውም ብዙ ተአምራትን ሠራ::
+አባቶች መነኮሳትም ማንነቱን ባወቁ ጊዜ ሰገዱለት:: ዶርታኦስ (ዱራታኦስ) በሚባል አንድ ደግ ሰው ቤትም በ6ኛው መቶ ክ/ዘ አጋማሽ አካባቢ የካቲት 14 ቀን ዐርፏል:: ዛሬ የታላቁ ሊቅ በዓለ ፍልሠቱ ነው::
=>አምላከ ቅዱሳን ይርዳን: ይቅርም ይበለን:: ከበረከታቸውም ያሳትፈን::
=>ታሕሳስ 10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ኒቆላዎስ ሊቅ
2.ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
3.ቅድስት ሱርስት ገዳማዊት
4.ቅዱስ ጥዋሽ ሕጽው
5.ቅዱሳን ተላስስና አልዓዛር
ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
2.አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
3.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ እልፍዮስ)
4.ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
5.ቅዱስ ዕፀ መስቀል
6.ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ
<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር
✝" ታኅሣሥ 10 "
<<< እንኩዋን ለቅዱሳን ሊቃውንት "አባ ኒቆላዎስ" : "አባ ሳዊሮስ" እና "ቅድስት ሱርስት" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ >>>
+*" ቅዱስ ኒቆላዎስ ሊቅ "*+
=>ቅዱስ ኒቆላዎስ:-
*ሃይማኖቱ የቀና::
*ምግባሩ የጸና ሊቅ::
*ብዙ መከራን የተቀበለ ሰማዕት::
*ብዙዎችን ያሳመነ ሐዋርያ::
*በበርሐ ለዘመናት የተጋደለ ጻድቅ::
*በዽዽስና ያገለገለ እረኛ እና:
*ከ318ቱ ሊቃውንት አንዱ ነው::
+የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ሲሆን ሃገሩ ሜራ ትባላለች:: ይህች ሃገር ዛሬ የት እንዳለች ማወቅ ባንችልም ታሪክ ግን የቀድሞዋ ሮም ግዛት እንደ ነበረች ይነግረናል:: የቅዱስ ኒቆላዎስ ወላጆች የዘመኑ ጥሩ ክርስቲያኖች ነበሩ::
+በሕጉ: በሥርዓቱ: በሥጋ ወደሙና በምጽዋት ቢኖሩም ልጅ አልነበራቸውም:: እግዚአብሔርን ሲለምኑ የጉብዝናቸው ዘመን አልፎ አረጁ:: ልጅ መጠየቁንም ተውት:: ልክ እነሱ መጠየቁን ሲያቆሙ ግን እግዚአብሔር ይሕንን ቅዱስ ፍሬ በዮና ማሕጸን ላይ ፈጠረ::
+እነርሱም ተገርመው ፈጣሪን እያመሰገኑ ተወለደ:: እንደ ተወለደ ግን ዓይናቸው ድንቅ ነገርን ተመለከቱ:: አትበው ሊያነሱት ሲጐነበሱ በራሱ ጊዜ ብደግ ብሎ ፈጣሪውን ሲያመሰግን ሰሙት::
+ለ2 ሰዓት ያሕልም ምንነቱን ያላወቁትን ጸሎት ሲያደርስ ቆየ:: መቼም የዕለት ሕጻን ይሕንን ማድረጉ እጅግ ድንቅ ነው:: ከዚህ በሁዋላም የሕጻኑ ቅዱስ ኒቆላዎስ አስገራሚ ነገሮቹ ቀጠሉ::
+ለምሳሌ:- በአጽዋማት: በረቡዕና በዓርብ ዕለታት 9 ሰዓት ካልሆነ የእናቱን ጡት አይጠባም:: ሁሌም ደግሞ የፈለገውን ያህል ቢፈስ የእናቱን የግራ ጡት አይጠባም ነበር:: ሁሌም የሚጠባው በስተቀኝ ያለውን ጡቷን ብቻ ነበር እንጂ::
+እንዲህ እንዲህ እያለ ቅዱስ ኒቆላዎስ አደገ:: እርሱ ወጣት በሆነ ጊዜ አረጋውያን ወላጆቹ ብዙ ሃብት: 400 የወርቅ ዲናርና የመሳሰለውን ትተውለት ዐረፉ:: እርሱ ግን ሁሉንም ትቶት በ16 ዓመቱ በርሃ ገባ::
+በዚያ ሲጾም: ሲጸልይ: ሲሰግድ ያዩ አበው ሁሉ ይገረሙ ነበር:: ሲሠራም: ሲታዘዝም: ሲሰግድም እንደ መንኮራኩር ፈጣን ነበርና:: በሕጻን ገላው ይሕንን ማድረጉ በእርግጥ ይደነቃል:: የቀናውን የሃይማኖት ትምሕርትንም ቶሎ በማጠናቀቁ ገና በ19 ዓመቱ ቀሲስ አድርገው ሾሙት::
+ቅስናን ከተሾመ በሁዋላ ተጋድሎውንም: አገልግሎቱንም አስፋፋ:: ካለበት ገዳም እየተነሳ ብዙ አካባቢዎችን በስብከት ያደርስ ነበር:: በወንጌል አገልግሎቱ ጊዜም ብዙ ተአምራትን ሲሠራ በተለይ በአንድ ቀን የአንድን አካባቢ ሕዝብ ጥቂት ሕብስትን እንደ ፈጣሪው አበርክቶ አብልቷል::
+የተረፈውም ብዙ መሶብ ተነስቷል:: (ዮሐ. 6:5) ጌታችን "በእኔ የሚያምን እኔ የምሠራውን እርሱ ደግሞ ይሠራል" ብሏልና:: (ዮሐ. 14:12) በተረፈም ፈዋሴ ዱያን: መንስኤ ሙታን ሆኖ ዘመናትን አሳልፏል::
+አንድ ቀን ግን በበአቱ እያለ የአንድ ሰውና የ4 ሴት ልጆቹ ነፍስ ሊጠፋ መሆኑ ይታወቀዋል:: ይሔውም በአቅራቢያው ባለ ከተማ የሚኖር አንድ ባለ ጠጋ ሃብቱ አልቆበት ተቸግሯልና ሰይጣን ክፉን እንዲሠራ ሹክ አለው:: ሰውየውም ለ4 ሴት ልጆቹ 4 ቤት አሰናድቶ በዝሙት ሊሸጣቸው ተዘጋጀ::
+ይሕንን በጸጋ ያወቀው ቅዱስ ኒቆላዎስ "ከመገስጽ መርዳት ይቀድማል" ብሎ: ማንም ሳያየው ወላጆቹ ከተውለት 400 የወርቅ ዲናር 100ውን ከፍሎ በሌሊት ከሰውየው በር ላይ ጥሎለት ተሰወረ:: ሰውየውም ተገርሞ የኃጢአት ሃሳቡን ተወ::
+ያ ሥራ ፈት ሰው ግን እንደ ገና ገንዘቡን በልቶ ተመሳሳይ ድርጊት ሊፈጽም ማሰቡን ቅዱሱ አወቀ:: አሁንም ተደብቆ 100 የወርቅ ዲናር ጣለለት:: ይህ ነገር 3ኛና 4ኛም ተደገመ:: በ4ኛው ግን ሰውየው ወደ ልቡናው ተመልሶ ይሕንን ያሕል ቸርነት የሚያደርግለትን ሰው ተደብቆ አየው::
+ሩጦም ሒዶ ከቅዱስ ኒቆላዎስ እግር ላይ ወደቀ:: "አባቴ! ነፍሴን ከእሳት አወጣሃት" አለው:: ቅዱሱም መልሶ መክሮ: ምሥጢሩን ግን ለማንም እንዳይናገር አሳስቦት ተመለሰ:: ያ ሰው ከዚያ በሁዋላ በጐ ክርስቲያን መሆን ችሏል::
+ለቅዱስ ኒቆላዎስ ግን አንድ ቀን ጌታችን: እመቤታችን: ቅዱስ መልአክ መጥተው ስጦታን አበረከቱለት:: መልአኩ ዙፋን: እመ ብርሃን የክብር ልብስን ሲሰጡት ጌታ ደግሞ ወንጌሉን ሰጠው::
+ወዲያውም አበው ካለበት በርሃ መጥተው የሜራ ዻዻስ እንዲሆን ሾሙት:: የተሾመበት ጊዜ ዘመነ ሰማዕታት ነበርና የሜራን ሕዝብ አጽንቶ ለሰማዕትነት በማብቃት ትልቁ ሃላፊነትም ተወጥቷል::
+ነገር ግን ዜና ሕይወቱ በነገሥታቱ ዘንድ ሲሰማ ለፍርድ አቀረቡት:: ስለ ክርስቶስ ሰብከሃል በሚል ስቃይና ሞት ተፈረደበት:: ወደ አውደ ስምዕ (የሰማዕታት አደባባይ) ወስደው ገረፉት: በእሳት አቃጠሉት: ደሙንም አፈሰሱት::
+ነገር ግን እግዚአብሔር ለሌላ ሙያ ይፈልገዋልና አልሞተም:: እነርሱ ግን በጭካኔ ለዘመናት አሰቃዩት:: በመጨረሻም እስር ቤት ውስጥ ጣሉት:: እርሱ በእስር ቤት ሳለም ዘመነ ሰማዕታት ተፈጸመ:: ቆስጠንጢኖስ ነገሠ::
+በዚህ ጊዜም ምዕመናን ቅዱስ አባታቸውን ከእስር ፈትተው በመንበሩ ላይ አኖሩት:: ለ13 ዓመታት ሕዝቡን ሲመራ ቆይቶ አርዮስ በካደ ጊዜ ወደ ኒቅያ አመራ:: በዚያም ለቅዱሳን ሊቃውንት 318ኛ ሆኖ ተቆጠረ:: በጉባኤው ፊትም ተአምራትን አሳየ::
+በኒቅያ ከባልንጀሮቹ ጋር አርዮስን አውግዞ: ሥርዓትን ሠርቶ: መጻሕፍትን ጽፎም ወደ ሃገሩ ተመልሷል:: በመንበሩ ላይ 40 ዓመታት ሲሞሉትም ዐርፎ በዚህች ቀን ተቀብሯል::
<<ኒቆላዎስ ማለት "መዋኤ ሕዝብ - ሕዝብን የሚያሸንፍ" ማለት ነው>>
+"+ ቅድስት ሱርስት +"+
=>ይህቺ ቅድስት እናት በዘመነ ጻድቃን ከተነሱ ስመ ጥር እናቶች አንዷ ናት:: ገና ከልጅነቷ በቤተ መንግስት ውስጥ ብታድግም ከመልካም እናቷ መልካምነትን ወርሳለች:: እጅግ በተቀማጠለ ኑሮ ውስጥ ሆና ሕይወቷን ክርስቶስን አልዘነጋችውም::
+ደም ግባቷ እጅግ የተወደደ ነበርና ገና በ12 ዓመቷ ለነገሥታቱ ልጆች ሚስት ትሆን ዘንድ ታጨች:: መቼም ሃብትን: ክብርን እንኩዋን እንዲህ በለጋ እድሜ አርጅተንም ቢሆን መናቁ አይሳካም::
+ቅድስት ሱርስት ግን አንድ ቅን ሃሳብ መጣላት:: ወደ አባቷ ዘንድ ሔዳም "ወደ አድባራት ሔጄ ከሠርጌ በፊት እንድሳለም ፍቀድልኝ" ስትል ጠየቀችው:: እርሱ ግን "ከሠርግሽ በሁዋላ ይደርሳል" ቢላት "በድንግልናየ ሳለሁ መቃብርህን እስማለሁ ብዬኮ ለፈጣሪየ ተስያለሁ" አለችው::
+አባቷም ከ300 ዲናር ወርቅና ከብዙ ሠራዊት ጋር ወደ ኢየሩሳሌም ላካት:: ቅድስቷ ሕጻንም በዚያ የጌታን መቃብር ተሳልማ ወታደሮችን ጠፋቻቸው:: ከዚያ በሁዋላ የት እንደ ደረሰች ያወቀ የለም:: ሱርስት ግን ከኢየሩሳሌም ግብጽ ወርዳ ወርቁ ገዳም እንዲታነጽበት አደረገች::
+እርሷ ግን መንኩሳ ወደ በርሃው ገባች:: በዚያም 27 ዓመት ሙሉ ማንንም ሳታይ: በጭንቅ: በመከራ: በአርምሞ ተጋደለች:: አንድ ቀን ግን ባሕታውያንን የሚመግብ ሲላስ የሚሉት ካህን አግኝቶ ዜናዋን ከነገረችው በሁዋላ ሰግዳ ዐርፋለች:: በ39 ዓመቷም በዚህች ቀን ቀብሯታል::
Photo unavailableShow in Telegram
✝እንኳን አደረሰነ!
✞በዓለ ቅዱሳን፦
✿በአሚን ተአማኒ (ሰማዕተ ጽድቅ)
✿እስትንፋሰ ክርስቶስ ዘአስጋጅ
✿በድላም ወአርምያ
✿ወዘካርያስ ካህን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡
https://t.me/zikirekdusn
✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 9th of Tahisas
1. St. Abba Poemin (Righteous and Martyr)
2. St. Armia
3. St. Zechariah✞✞✞ Monthly Feasts
1. The “318” Holy Scholars (Fathers assembled at the Council of Nicaea)
2. Abba Barsauma the Syrian (Father to all Syrian Monks)
3. Abune Estenfase Kirstos (Ethiopian)
4. Saints of the Realm of the Blessed
5. Abba Melchizedek of Mida (Ethiopian)
6. St. Zosimus (Zocima), Righteous (A father who saw the Realm of the Blessed)
✞✞✞“ I write unto you, fathers, because ye have known him that is from the beginning. I write unto you, young men, because ye have overcome the wicked one. I write unto you, little children, because ye have known the Father. I have written unto you, fathers, because ye have known him that is from the beginning. I have written unto you, young men, because ye are strong, and the word of God abideth in you, and ye have overcome the wicked one.”✞✞✞
1 John 2:13-14
✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞
(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
