አዲስ ነገር መረጃ
رفتن به کانال در Telegram
#አዲስ_ነገር_መረጃ #መረጃዎች_በትኩሱ ና ሳይዉሉ እንዲሁም ሳያድሩ በቻናሉ በኩል ይደርሳሉ Addis Ababa , Ethiopia Buy Ads : https://telega.io/?r=UbutLo2z #ለአስተያየት እና ለማስታወቂያ ስራዎች 👇👇 @Addisnegermereja_bot
نمایش بیشتر2025 سال در اعداد

103 444
مشترکین
-4824 ساعت
+3257 روز
+15430 روز
آرشیو پست ها
Photo unavailableShow in Telegram
"የእስራኤልን እርምጃ መግታት አልችልም" ትራምፕ
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅና ማስቆም እንደማይችሉ ተናገሩ።
ትራምፕ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ "የእስራኤልን እርምጃ መግታት አልችልም" ብለዋል።
ፕሬዚዳንቱ "ለመናገር ያክል አስተያየት የለኝም" ሲሉ ዝርዝር ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
አሜሪካ ለሶማሊላንድ እውቅና ለመስጠት ያላትን ፍላጎት በተመለከተ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ "እኛ እያሰብንበት ነው፣ ሁሌም ትልቅ ውሳኔዎችን ነው የማሳልፈው፣ ደግሞም ትክክል ይሆናሉ" በማለት ተናግረዋል።
"የሶማሊላንድ ጉዳይ እንደምታውቁት ውስብስብ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል። #newsmax
@Addis_News
@Addis_News
👍 23🤪 5❤ 2
01:08
Video unavailableShow in Telegram
👉 ከ8 በላይ ሳይቶችን ገንብቶ ያስረከበው
ቴምር ፕሮፐርቲ
አሁንም በድጋሜ አዳዲስ ሳይቶችን
ለሽያጭ አቅርቧል ።
📍 ሳር ቤት
#በ35%ቅናሽ! (በ100% ክፍያ)
👉 ባለ 2 መኝታ = 81ካሬ = 5.7ሚ
👉 ባለ 2 መኝታ = 106ካሬ = 7.9ሚ
👉 ባለ 3 መኝታ = 139ካሬ = 10.3ሚ
👉 ባለ 3 መኝታ = 153ካሬ = 11.4ሚ
#በ20% ቅድመ ክፍያ (በግንባታ ሂደት ለሚከፍሉ)
👉 81ካሬ = ሙሉ ክፍያ = 9.3ሚሊዮን
ቅድመ ክፍያ = 20% (1.8ሚሊዮን)
👉 106ካሬ = ሙሉ ክፍያ = 12.1ሚ
ቅድመ ክፍያ = 20% (2.4ሚሊዮን)
👉 139ካሬ = ሙሉ ክፍያ = 15.9ሚ
ቅድመ ክፍያ = 20% (3.1ሚሊዮን)
📍 አዋሬ
#በ35%ቅናሽ! (በ100% ክፍያ)
👉 ባለ 1 መኝታ = 78ካሬ = 5.5ሚሊዮን
👉 ባለ 3 መኝታ = 117ካሬ = 8.3ሚሊዮን
👉 ባለ 3 መኝታ = 137ካሬ = 9.7ሚሊዮን
👉 ባለ 3 መኝታ = 145ካሬ = 10.3ሚሊዮን
#በ20% ቅድመ ክፍያ (በግንባታ ሂደት ለሚከፍሉ)
👉 78ካሬ = ሙሉ ክፍያ = 8.5ሚሊዮን
ቅድመ ክፍያ = 20% (1.7ሚሊዮን)
👉 135ካሬ = ሙሉ ክፍያ = 14.8ሚሊዮን
ቅድመ ክፍያ = 20% (2.9ሚሊዮን)
👉 157ካሬ = ሙሉ ክፍያ = 17.2ሚሊዮን
ቅድመ ክፍያ = 20% (3.4ሚሊዮን)
⩩ ቀሪውን 80%፤ በግንባታ ሂደት፤ ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ፤ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት።
⩩ 30% እና ከዚያ በላይ ለሚከፍሉ፤ ከከፈሉት ላይ ከ15 -25% ቅናሽ አዘጋጅተናል።
ለበለጠ መረጃ ;- 0940464607
0994003949
25.16 MB
❤ 4
Photo unavailableShow in Telegram
ምድር በጎርፍ ትጠፋለች በማለት በኖህ መርከብ በተመሰለችው መርከብ በሺዎች ያሳበሰበው የጋናው ነቢይ የጥፋቱ ቀን ተራዝሟል አለ።
በጋና ኩማሲ ወደ አራት ሺ ሰው ገና ተሰርታ ባላለቀችው መርከብ ከምድር ጥፋት ለመዳን የመጣ ሲሆን የጋናው ነቢይ እቦህ ኖህ ሁሉም ሰው ወደየሀገሩና ወደየመንደሩ እንዲመለስ ነግሯል።
"ዛሬ ዓለም አያበቃላትም" ብሏል።
ለ21 ቀናት ከጸለየና ከጦመ በኋላ፣ አምላክ ለሕዝቦቹ ጊዜ እንዲሰጣቸው እንደተማጸነና አምላክም ጸሎቱን ሰምቶ የጥፋቱን ቀን እንዳራዘመው ገልጿል።
"ይህ ሀሰተኛ ነቢይ ነው" የሚል ትችት የቀረበበት ነቢይ፥ ከ“እግዚአብሔር ሰዎች” ጋር ካደረገው ጸሎት በኋላ፣ እግዚአብሔር ሁሉንም ሰው የሚያስተናግዱ ተጨማሪ መርከቦች እንዲገነቡ ተጨማሪ ጊዜ እንደፈቀደላቸው ገልጿል።
@seledadotio
@seledadotio
🤣 92❤ 14
Photo unavailableShow in Telegram
የአፍሪካ ህብረት እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅናን ውድቅ አደረገ
የአፍሪካ ህብረት ለሶማሊያ አንድነት እና ሉዓላዊነት ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት አለው ብሏል ባወጣው መግለጫ።
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ በሶማሊላንድን በተሰጠ እውቅና ላይ ከባድ ስጋት አለኝ ብለዋል።
የኮሚሽኑ ሊቀመንበር በአፍሪካ ህብረት መስራች ህግ መርሆዎች ላይ የተመሰረተውንና በተለይም በ1964ቱ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ውሳኔ የጸደቀውን "ከነጻነት በኋላ የተወረሱ ድንበሮች የማይደፈሩ የሚለውን የቆየና ጽኑ የአፍሪካ ህብረት አቋምን እደግፋለው ብለዋል።
ሊቀመንበሩ ሶማሊላንድ የሶማሊያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ አካል ናት በማለት ሶማሊላንድን እንደ ገለልተኛ አካል እውቅና ለመስጠት የሚደረጉ ማናቸውንም ውጥኖች ወይም እርምጃዎች ውድቅ አድርገዋል።
❤ 16🤣 8😨 2💔 1
Photo unavailableShow in Telegram
ሰሜን ኮሪያ እና ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት ውስጥ ደምን፣ ሕይወትን እና ሞትን ተጋርተዋል ሲሉ ኪም ጆንግ ኡን ተናገሩ
የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ለሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ባስተላለፉት የአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤ ሰሜን ኮሪያና ሩሲያ በዩክሬኑ ጦርነት ውስጥ "የደም፣ የሕይወት እና የሞት" ትስስር አላቸው ብለዋል።
በሰሜን ኮሪያ የዜና ወኪል በታተመው በዚህ መልዕክት፤ ኪም 2025 በፒዮንግያንግ እና በሞስኮ መካከል ያለው ጥምረት "በአንድ ቦይ ውስጥ በጋራ በፈሰሰ ደም፣ በሕይወት እና በሞት" የጠነከረበት "በእውነትም ትርጉም ያለው ዓመት" ነው ብለዋል።
የደቡብ ኮሪያ እና የምዕራባውያን የስለላ ድርጅቶች ፒዮንግያንግ በዩክሬን ጦርነት ከሞስኮ ጎን ተሰልፈው እንዲዋጉ በሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችን መላኳን ቀድመው ዘግበው ነበር። ሰሜን ኮሪያ ባለፈው አመት ሚያዚያ ወር ላይ ወታደሮቿ የሩሲያን ወታደራዊ ዘመቻ ለመደገፍ መሰማራታቸውን እና አንዳንዶቹም በውጊያው ላይ መገደላቸውን አረጋግጣለች።
በታህሳስ ወር መጀመሪያ ላይ ፒዮንግያንግ በነሐሴ ወር ውስጥ ከዩክሬን ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው የኩርስክ ክልል ፈንጂዎችን ለማጽዳት ወታደሮችን ልካ እንደነበር አምናለች።
ወታደራዊ ክፍሉ ወደ ሀገር ሲመለስ ታህሳስ 4 ቀን ኪም ባደረጉት ንግግር፥ በ120 ቀናት ቆይታቸው ቢያንስ ዘጠኝ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች መገደላቸውን ተናግረዋል።
@Addis_News
@Addis_News
❤ 17👏 9🤣 4
Photo unavailableShow in Telegram
🌟🌟ታላቅ የገና በዓል ቅናሽ በካሬ 78,000 ብር
✅እንዲሁም ሙሉ ክፍያ ለሚከፊል በካሬ 54,800
🔷 በ10 % ቅድመ ክፍያ
🔷 50 % የባንክ ብድር የተመቻቸለት
📍Location እንግሊዝ ኢንባሲ አጠገብ ውብ እይታ (Top View) ያላቸው ቤቶች በሽያጭ ላይ እንገኛለን
👉ከባለ 2 መኝታ- ባለ4 መኝታ
✅ ህንፃው ላይ ያሉ ተጨማሪ አገልግሎትች
👉5 ሰፋፊ ሊፍት /elevator
👉የቆሻሻ መጣያ/garbage chute
👉አውቶማቲክ ጀኔረተር/ automatic generator
👉ሰገነት/terrace
👉የመኪና ማቆምያ/car parking
👉 ጂም , እስፖ
👉 የዋና ገንዳ
👉 የልጆች መጫወታ
✨ባለ 2 መኝታ
138 ካሬ
157.3 ካሬ
163.6 ካሬ
✨ባለ 3 መኝታ
152.4 ካሬ
158.1 ካሬ
187.6 ካሬ
211.5 ካሬ
✨ባለ 4 መኝታ
240.7 ካሬ
258.4 ካሬ
📞 ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
0973559591
0919489575
Telegram -@Homef17
https://t.me/lijhop7
❤ 7
Photo unavailableShow in Telegram
በጃፓን አንድ የ38 ዓመት ሰው በቢላ በፈጸመው ጥቃት 15 ሰዎች ቆሰሉ
ጥቃቱ የደረሰው በሚሺማ ከተማ በጎማ ፋብሪካ በሚሰሩ ሰራተኞች ላይ ነው።
እንደ ማይኒቺ ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ትናንት አርብ በደረሰው ጥቃት ስምንት ሰዎች በቢላዋ ሲወጉ፣ ሰባት ሌሎች ደግሞ ሰውዬው በረጨባቸው ፈሳሽ ተጎድተዋል።
ጥቃቱን ፈጽሟል ተብሎ የተጠረጠረው የ38 ዓመቱ ማሳኪ ኦ. በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን፣ በግድያ ሙከራ ወንጀል ምርመራ እየተካሄደበት ይገኛል።
እንደ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች ከሆነ፣ ግለሰቡ ጥቃቱን ሲፈጽም ጭንብል አድርጎ የነበረ ሲሆን፣ እንደ ክሎሪን/በረኪና ያለ ፈሳሽም ሰራተኞቹ ላይ ረጭቷል።
በጃፓን እንዲህ ያሉ ከባድ የኃይል ድርጊቶች እምብዛም የተለመዱ አይደሉም።
በምሥራቅ እስያዊቷ ሀገር ጃፓን የጦር መሣሪያ ቁጥጥር በጣም ጥብቅ ነው። ሆኖም ግን፣ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በሕዝቡ ዘንድ መረበሽን የፈጠሩ በርካታ የቢላዋ ጥቃቶች ተከስተዋል።
@Addis_News
@Addis_News
❤ 9🙏 3🥰 1
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “እግዚእ ወገብር፤ አምላክ ሰው ሆነ፣ ሰው አምላክ ሆነ” ማለት ነው፡፡
ቅዱስ ገብርኤል የጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መምጣትና ሰው መሆን ለመናገር ተልኮ የምሥራች ዜናን ያበሠረ፤ በዲያቢሎስ የተንኮል ወጥመድ ገብተው ለተሰናከሉት ፈጥኖ ለመርዳት የሚደርስ፣ በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩት ሁሉ የብርሃን ፋና ያበራ፣ ሰብአ ሰገልን የመራ መልአክ ነው፡፡
ከቀድሞ ጀምሮ ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር ተልከው መንፈስ ቅዱስ እንዳናገራቸው ዓለምን ስለማዳን ከጽዮን የሚወጣ ከያዕቆብ በደልን የሚያርቅ ጌታ “ይወርዳል ይወለዳል” በማለት በየወገናቸውና በየዘመናቸው የተናገሩትን የነቢያትን ትንቢት መፈጸሙን የሚያበስረውን የምሥራችን ቃል የተናገረ ነው፡፡ የጨለማ አበጋዝ በሆነ በሰይጣን ተንኮል በሰው ልቦና ውስጥ አድሮ የነበረውን ከእፉኝት መርዝ የከፋ የኀዘን ስሜት ያጠፋ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡
ቅዱስ ገብርኤል ከሌሎች መላእክት ተለይቶ ዘወትር በምንጸልያቸው ጸሎቶች ስሙ የሚጠራ መልአክ ነው፡፡ ይኸውም በዘወትር ጸሎቶች በአቡነ ዘበሰማያት፣ በሰላመ ቅዱስ ገብርኤል፣ በውዳሴ ማርያም፣ በይዌድስዋ መላእክትና በመሳሰሉት ጸሎቶች ዘወትር ስሙ የሚጠራ ነው፡፡ ካህናት አባቶች ቅዱስ ገብርኤል ስእለት ሰሚና ፈጥኖ ደራሽ መልአክ እንደሆነ ይነግሩናል፡፡ ይኽም በክርስቲያኖችም ዘንድ እጅግ ተወዳጅ እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ፈጥኖ ደራሹ መልአክ፣ ስእለት ሰሚው መልአክ ይሉታል፡፡ የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከሌሎች መላእክት ሁሉ በይበልጥ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን እንደምትወደው በድርሳነ ገብርኤል “ወንድሞቻችን ሆይ፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከመላእክት ሁሉ ይልቅ ቅዱስ ገብርኤልን በይበልጥ እንደምትወደው ተመልከቱ፤ የልጅዋን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ከእርሷ መወለድ ያበሠራት እርሱ ነውና” የሚል ተጽፎ ይገኛል፡፡
ከሰባቱ ሊቃነ መላእክትም አንዱ በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ይህ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ በተረዳኢነቱና በአማላጅነቱ፣ ያዘኑትን ለማጽናናት የምሥራች ለመንገር ከእግዚአብሔር ወደ ምእመናን ይላካል፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን አባቶቻችን እንዳስተማሩን በዘመኑ ጣኦት የሚያመልከው ንጉስ ናቡከደነፆር በባቢሎን ምርኮ የወሰዳቸውን የእግዚአብሔር ሰዎች አናንያ፤ አዛርያ፤ ሚሣኤል እጅግ ይወዳቸው ነበር፡፡ ከባቢሎናውያን ይልቅ ጠቢባን የነበሩት ሶስቱ ሕጻናት በትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ሦስት ሰፍሮ የምናገኘው ታሪካቸው እንደሚነግረን ንጉሱ የጣኦት ምስል አሰራ በገሊላ አውራጃ ያለውን ሕዝብ ጠርቶም ለጣኦቴ ያልሰገደ ወደ እሳት ውስጥ ይጣላል ብሎ አወጀ። የንጉስ ትህዛዝ ነውና ሕዝቡ ሁሉ ለጣኦቱ ሲንበረከክ እነርሱ ግን ቆመው ያዩ ነበር።
ናቡከደነፆር እርሱ ላስቆመው ጣኦት አለመስገዳቸውን ሲሰማ ተናደደ፣ ተበሳጨም እሳቱን 7 እጥፍ እንዲነድ አስደረገ ሦስቱንም አስሮ እሣቱን እያሳየ "ከመቃጠል ወይስ ለእኔ ጣኦት መስገድ የቱ ይሻላል?" ቢላቸውም የእግዚአብሔር የሆነ ሰው ምንም ነገር አያስፈራውምና "የምናመልከው አምላካችን ከሚነደው ከእሳቱ እቶኑ ሊያድነን ይችላል፣ ባያድነንም ግን አንተ ላቆምከው ጣኦት አንሰግድም" አሉት፡፡ በዚህ ጊዜ ጉልበት ያላቸው ሠዎች ተፈልገው ሦስቱን ወጣቶች አስረው ወደ እሳት ቶን ውስጥ ጣሏቸው አስረው የጣሏቸውን ወታደሮች የእሳቱ ወላፈን አቃጠላቸው ሠለስቱ ደቂቅን ግን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ እሳቱን አበረደላቸው፣ አጠፋላቸው። ከእሳቱ ላይ ሆነውም እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡
ገዳማውያኑም ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ሲሉት ይደርስላቸዋ፤ በረከታቸው አብሮን እንዲሆን ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
❤ 55👍 6
በጫማው ውስጥ ጫት ደብቆ ወደ ማረሚያ ቤት ለማስገባት የሞከረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
በሀላባ ዞን ማረሚያ ተቋም ውስጥ የሚገኝን ታራሚ ለመጠየቅ የሄደ ግለሰብ፣ ጫት በጫማው ውስጥ ደብቆ ለማስገባት ሲሞክር እጅ ከፍንጅ መያዙ ተነገረ።
አቶ መሳይ ፊቻጎ የተባለው ግለሰብ፣ ለታራሚ በርገና ሀንድኖ እንዲደርስ ግምቱ 1,000 (አንድ ሺህ) ብር የሚሆን ጫት በጫማው ውስጥ በመደበቅ የፍተሻ ጣቢያውን ለማለፍ ሞክሮ ነበር።
ይሁን እንጂ በተቋሙ የፍተሻ ኦፊሰር በዋና ሳጅን አሸናፊ አበጋዝ በተደረገ ጥብቅ ፍተሻ ድርጊቱ ሳይሳካ ቀርቷል።
የተቋሙ ኃላፊ ኢንስፔክተር ሁሴን ጉንታ እንደገለጹት፣ ግለሰቡ ከጠያቂዎች ጋር በመቀላቀል ደብቆ ለማስገባት የሞከረው ጫት ወደ ታራሚዎች ሳይገባ መከላከል ተችሏል። ኃላፊው አክለውም፦
"ህብረተሰቡ የማረም እና የማነጽ ስራን ከሚያሰናክሉ መሰል ተግባራት ሊቆጠብ ይገባል። ታራሚዎች ከሱስ ነፃ ሆነው ውጤታማ ዜጋ እንዲሆኑ የሁሉንም ትብብር እንሻለን" ብለዋል።
ተቋሙ መሰል ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ቁጥጥሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል።
ምንጭ :- ሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ ማረሚያ ተቋም
@seledadotio
@seledadotio
🤣 21❤ 19🥱 2
Photo unavailableShow in Telegram
🇪🇹💸💸📱 በOnline ስራ በቀን ከ 2ሺ ብር ጀምሮ የሚሰሩበት ድንቅ የስልክ መትግበሪያ (Application)። ዳውንሎድ አርገው ተመዝግበው ከቤትዎ ሆነው ስራ ይጀምሩ።
💥💰በቀላሉ ከታች ባለው ሊንክ አፑን ዳውንሎድ በማድረግ መስራት እና መጠቀም ትችላላችሁ።
✅Download ለማድረግ
👇👇👇👇👇👇👇
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.habeshanjobs.habeshanjobs
❤ 6🤣 4🔥 1
የመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን በሃይማኖት ሚዲያዎች ላይ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጠ::
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን የተሰጣቸውን የፈቃድ ገደብ አክብረው፣ በጥንቃቄ እና በሃላፊነት ስሜት እንዲሰሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳሰበ።
ባለስልጣኑ በመግለጫው እንደገለጸው፣ የጂፒኤስ (GPS) የቴሌቪዥን ጣቢያ በሀገራችን ሰላሌ አካባቢን በተመለከተ ተገቢ ያልሆነ እና ከአሰራር ደንብ ውጭ የሆነ መረጃ ማሰራጨቱ ተረጋግጧል። በዚህም ምክንያት ለጣቢያው ጥብቅ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን አስታውቋል።
ማስጠንቀቂያው የተሰጠው "ጂሰስ ኘሮፌቲክ ስኘሪት ቸርች" በቀን 13/04/2018 በማህበራዊ ገጾቹ ያሰራጨው ፕሮግራም የመገናኛ ብዙሃን አዋጅን የጣሰ ሆኖ በመገኘቱ እንደሆነ ተገልጿል።
በአዋጁ መሰረት ማንኛውም የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን አስተምህሮቶቻቸውን ለምዕመናን እንዲያደርሱ ፍቃድ ቢሰጣቸውም፣ የተቀመጡ ህጎችን ጥሰው በሚገኙት ላይ ባለስልጣኑ አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ አሳስቧል። በመሆኑም ሁሉም የሚዲያ ተቋማት ያለባቸውን ማህበራዊ ሃላፊነት ተረድተው እንዲንቀሳቀሱ ጥሪ ቀርቧል።
ይህ መረጃ ጠቃሚ ሆኖ ካገኙት ለሌሎች እንዲደርስ 'Share' ያድርጉት።
Vi Ethiopia Media Authority- ኢመብባ
❤ 31👏 5💔 2
ፌስቡክ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በሌላ ሃገር ተጠቃሚዎች ላይ ያለ አግባብ ገደብ እየጣለ መሆኑ ተገለጸ
በዓለም አቀፉ የማህበራዊ ሚዲያ ግዙፍ ኩባንያ ፌስቡክ (ሜታ) ሌሎች ሃገሮችን ጨምሮ በበርካታ ኢትዮጵያውያን ተጠቃሚዎች እና የሚዲያ ገጾች ላይ ያለ አግባብ የእንቅስቃሴ ገደብ እና የማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን እየላከ መሆኑ ታውቋል። በተለይም ባለፉት ጥቂት ቀናት በርካታ ተጠቃሚዎች የፌስቡክን የህብረተሰብ ደህንነት ደንቦች መጣሳቸውን የሚገልጹ እና Human Exploitation የሚሉ ይዘቶች መለጠፋቸውን የሚጠቁሙ መልዕክቶች በተደጋጋሚ እየደረሷቸው መሆኑን ቅሬታቸውን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።
ይህ ችግር በስፋት እየታየ ያለው ምንም አይነት የህግ ጥሰት ባልፈጸሙ ተራ ተጠቃሚዎች እና ህጋዊ የዜና ተቋማት ላይ ሲሆን፣ ፌስቡክ ፖስቶቹን መጀመሪያ ካነሳ በኋላ በጥቂት ሰዓታት ወይም ቀናት ልዩነት "ስህተት መሆኑን አረጋግጠናል" በማለት ይዘቶቹን ወደ ነበሩበት እየመለሰ ይገኛል። ይህም የኩባንያው አውቶሜትድ የመቆጣጠሪያ ሲስተም (AI) የቃላት ትርጉም ስህተት እየሰራ መሆኑን የሚያመላክት ነው ተብሏል።
ባለሙያዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ፣ እንዲህ አይነቱ የጅምላ ገደብ በሃገራቶች ካለው ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና ስሱ ቃላትን ከመጠቀም ጋር ተያይዞ ሊከሰት ይችላል። ሲስተሙ እንደ "እስራት"፣ "ግድያ" ወይም "ጦርነት" ያሉ ቃላትን እንደ መረጃ ከመቁጠር ይልቅ እንደ ህግ ጥሰት በመፈረጅ ለገጾች መታገድ ምክንያት እየሆነ ይገኛል ተብሏል።
ተጠቃሚዎች እንዲህ አይነት ማስጠንቀቂያ ሲደርሳቸው "ውሳኔውን አልቀበልም" (Disagree with Decision) የሚለውን አማራጭ በመጫን ይግባኝ ማለት እንዳለባቸው እና የአካውንታቸውን ደህንነት በየጊዜው እንዲፈትሹ የዘርፉ ባለሙያዎች ምክራቸውን እየለገሱ ነው።
ሜታ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ተጠቃሚዎች ላይ ለሚታየው ለዚህ ተደጋጋሚ ስህተት የሰጠው ይፋዊ ምላሽ ባይኖርም፣ ችግሩ ግን በበርካታ ተጠቃሚዎች ዘንድ ስጋትን መፍጠሩን ቀጥሏል።
@Addis_News
@Addis_News
❤ 2😢 2🤪 2
